Worldathletics2024

ኢትዮጵያ በዓለም ወጣቶች አትሌቲክስ ውድድር አራት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

ኢትዮጵያ በዓለም ወጣቶች አትሌቲክስ ውድድር አራት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

በደቡብ አሜሪካዋ ፔሩ ሊማ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ውድድር ትናንት ጠናቋል፡፡ በዚህ የአትሌቲክ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከአሜሪካ በመቀጠል ከዓለም ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች፡፡ ኢትዮጵያን በመወከል የተሳተፈው ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ብሔራዊ ቡድን በ6 ወርቅ፣ 2 ብር እና 2 ነሐስ በአጠቃላይ 10 ሜዳሊያዎችን ማሸነፍ ችሏል። በዚህ ኢትዮጵያ ከዓለም አሜሪካን በመከተል 2ኛ እንዲሁም ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን ያጠናቀቀች ሲሆን፤ ውድድሩን 1ኛ ደረጃ በመያዝ ያጠናቀቀች አሜሪካ በ8 ወርቅ፣ 4 ብር እና 4 ነሃስ በድምሩ 16 ሜዳሊያዎችን አግኝታለች። ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ አትሌቶች በአትሌት መዲና ኢሳ በ5000 ሜትር፣ በአትሌት ሲምቦ አለማየሁ በ3000 ሜትር መሰናክል በአትሌት ጀነራል ብርሃኑ በ800 ሜትር፣ በአትሌት…
Read More
ኢትዮጵያ በግላስኮው የዓለም ቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድርን በአምስተኛነት አጠናቀቀች

ኢትዮጵያ በግላስኮው የዓለም ቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድርን በአምስተኛነት አጠናቀቀች

በስኮትላንድ ግላስጎ ሲካሄድ የቆየው የ2024 የአለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ፍጻሜውን አግኝቷል። ከየካቲት 22 እስክ 24 2016 ዓ.ም ሲካሄድ በነበረው የ19ኛው የዓለም የቤት ዉስጥ ሻምፒዮና ከ130 በላይ ሀገራት  የተውጣጡ ከ650 በላይ አትሌቶቸ  መሳተፋቸው ተነግሯል። ኢትዮጵያ በ800 ሜትር፣ በ1500 ሜትር እና በ3000 ሜትር  በሴትና በወንድ  በአጠቃላይ  በ8 ሴቶች እና በ5 ወንዶች በድምሩ በ13 አትሌቶች መሳተፏን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በሻምፒዮናው በሴቶች 800 ሜትር ፅጌ ዱጉማ እና በሴቶች 1500 ሜትር ፍሬወይኒ ሀይሉ የወርቅ፣ በሴቶች 3000 ሜትር ጉዳፍ ፀጋዬ የብር እንዲሁም በወንዶች 3000 ሜትር ሰለሞን ባረጋ የነሃስ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ያስገኙ አትሌቶች ሆነዋል። በዚህ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ  ሁለት ወርቅ አንድ ነሀስ በአንድ ብር…
Read More