ዜና

ጦርነቶች እንዲቆሙ በማደራደር የሚታወቁት ዲፕሎማት በ100 ዓመታቸው ህይወታቸው አለፈ

ጦርነቶች እንዲቆሙ በማደራደር የሚታወቁት ዲፕሎማት በ100 ዓመታቸው ህይወታቸው አለፈ

የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ ሄንሪ ኪሲንገር   በመቶ አመታቸው  አረፉ ታዋቂው ዲፕሎማት እና ተፅዕኖ ፈጣሪ የውጭ ፖሊሲ አሳቢ በኮነቲከት በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ትናንት ለሊት መሞታቸውን የአማካሪ ድርጅታቸው ኪሲንገር አሶሺየትስ በመግለጫው ገልጿል። በፈረንጆቹ በ1969 የፕሬዝዳንት ሪቻርድ ኒክሰን ከፍተኛ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ከመሆናቸው በፊት በሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪ አግኝተው አለም አቀፍ ግንኙነቶችን አስተምረዋል። የፕሬዚዳንት ጄራልድ ፎርድ የመንግስት ፀሀፊም ሆነው አገልግለዋል። ጎበዝ ተደራዳሪ ተብለው የተወደሱ ሲሆን በ1970ዎቹ አሜሪካ ከሶቪየት ኅብረት ጋር ያለውን ግንኙነት እንድትሻሻል  ኪስንገር ትልቅ ሚና ነበራቸው። አሜሪካ  ከቻይና ጋር ያላትን ግንኙነት የተሻለ ለማድረግ መንገድ ጠርገዋል። እ.ኤ.አ. በ 1973 ኪሲንገር የፓሪስ የሰላም ስምምነትን በማሳካታቸው  ከዲፕሎማት ለዱክ ቶ…
Read More
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በሚካሄደው የቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስታውቋል፡፡ አትሌቱ በፌስቡክ ገጹ እንዳለው "ከብዙ ጊዜ ጉዳት በኋላ በቫሌንሺያ ማራቶን እሳተፋለሁ" ብሏል። "ከብዙ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር በመመለሴ ደስተኛ ነኝ" ያለው አትሌት ቀነኒሳ አኤኤንቲኤ የተሰኘው ኩባንያ ስፖንሰሬ ነው፣ ላደረገልኝ ድጋፍ አመሰግናለሁ " ሲልም ገልጿል። ውድድሩ የፊታችን ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በስፔኗ ቫሌንሲያ እንደሚካሄድ ተገልጿል። አትሌት ቀነኒሳ በአምስት እና አስር ሺህ ውድድሮች ላይ ለዓመታት ሳይረታ የቆየ ውጤታማ አትሌት ሆኖ ቆይቷል። በሁለቱም ርቀቶች የዓለም ሪከርዶችን ለ16 ዓመታት ይዞ የቆየው አትሌት ቀነኒሳ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ፊቱን ወደ ማራቶን ውድድር አዙሯል። የማራቶን ውድድርን ከሁለት ሰዓት በታች ይገባል ተብሎ ከሚጠበቁት…
Read More
በአዲስ አበባ 100 ሺህ ሰዎች የሚሳተፉበት ሰላማዊ ሰልፍ ተጠራ

በአዲስ አበባ 100 ሺህ ሰዎች የሚሳተፉበት ሰላማዊ ሰልፍ ተጠራ

የኢትዮጰያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ እንደገለጸው መነሻውን አራት ኪሎ ያደረገ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለከንቲባ ቢሮ ማስገባቱን ገልጿል፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ "ጦርነት ይቁም! ሠላም ይስፈን፣ መከላከያ ሰራዊቱ ባስቸኳይ ወደ ካምፕ ይግባ!" በሚል መሪ ቃል እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚካሄደውን ደም አፋሳሽ ጦርነት ለማስቆም በሚል የተዘጋጀው ይህ ሰላማዊ ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ. ም በሀገሪቱ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ይካሄዳል ተብሏል፡፡ የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪዎች ደብዳቤውን ጦርነት እንዲቆም፣ መከላከያ ሠራዊቱ ከዘመተባቸው ክልሎች ወጥቶ ወደ ጦር ካምፑ እንዲመለስና ፖለቲካዊ ውይይቶች እንዲከፈቱ በሰልፉ ላይ እንጠይቃለንም ብለዋል፡፡ የኢትዮጰያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ /ኢህአፓ/ እና ሌሎች ዜጎች አስተባባሪነት የተጠራው ይህ ሰላማዊ ሰልፍ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት…
Read More
በጦርነት በተጎዳችው ትግራይ የ6 ቢሊዮን ብር ብረት ማምረቻ ፋብሪካ ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

በጦርነት በተጎዳችው ትግራይ የ6 ቢሊዮን ብር ብረት ማምረቻ ፋብሪካ ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

በ6 ቢሊዮን ብር ወጪ በኢትዮጵያ እና ቻይና ባለሃብቶች ትብብር የብረታ-ብረት ማምረቻ ኢንዱስትሪ በመቐሌ ከተማ ሊገነባ ነው። በአስር ወራት ውስጥ የሚገነባው ይህ ኢንዱስትሪ የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ዛሬ ይፋ ተደርጓል። በዚህ ወቅት የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ፤ የሌጀንድ ብረታብረት ኢንዱስትሪ ሃላፈነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር በመሆኑ አስፈጊው ድጋፍ ይደረግለታል ብለዋል። ሌሎች በግልና በማህበር የተደራጁ ባለሃብቶችም የዚህን የልማት ፕሮጀክት አርአያ ተከትለው በማልማት  ራሳቸውንና ሀገራቸውን እንዲጠቅሙ መልእክት አስተላልፈዋል። የብረታብረት ማምረቻው 75 በመቶ በኢትዮጵያዊው ባለሃብት ኢንጅነር ያሬድ ተስፋይ የተሸፈነ ሲሆን ቀሪው 25 በመቶ ደግሞ በቻይናዊው ባለሃብት ሚስተር ሊ ዮን መሸፈኑን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሳምሶም ገብረመድህን ገልጸዋል።…
Read More
ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር እንደገለጸው ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በግንባታ ላይ ካሉት የመስኖ ግድቦች ውስጥም 13ቱን በተያዘው የ2016 ዓመት በከፊል ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ በዚህ ዓመት እንዲጠናቀቁ በሚል እየተገነቡ ላሉ ግድቦችም 8 ነጥብ 03 ቢሊዮን ብር መመደቡ ተመልክቷል፡፡ የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት እንደገለጹት በአሁኑ ጊዜ በሀገሪቱ 28 የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታቸው በመከናወን ላይ ነው፡፡ 13 የመስኖ ፕሮጀክቶች በከፊል ሲጠናቀቁ 2 ሺህ 450 ሄክታር መሬት ማልማት የሚያስችሉ እንደሆኑም ሃለፊው ተናግረዋል፡፡ እየተገነቡ ካሉት ግድቦች በተጨማሪም 27 አዲስ የመስኖ ግድቦችን ለመገንባት የጥናትና ዲዛይን…
Read More
የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ስለባህር በር አስተያየት ሲሰጡ እንዲጠነቀቁ ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ስለባህር በር አስተያየት ሲሰጡ እንዲጠነቀቁ ተጠየቀ

ባለስልጣናት ስለ ባህር በር ጉዳይ የሚሰጡት መግለጫ የተጠናና ጥንቃቄ የተሞላበት መሆን እንዳለበት ምሁራን አሳስበዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የባህር በር ዙሪያ የምሁራን ውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ በዚህ የምሁራን መድረክ ላይ ጥናት ያቀረቡና ውይይት ያደረጉ ምሁራን፣ መንግሥት ስለባህር በር የሚሰጣቸው መረጃዎች የጎረቤት አገሮችን የማያሠጉና ጥንቃቄ የተሞላባቸው እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡ ‹‹ፍትሐዊ የወደብ አጠቃቀም ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና ልማት›› በሚል ርዕስ በተስተናገደው በዚህ ዓውደ ጥናት ላይ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ባለቤት መሆን ስለምትችልባቸው አማራጮች ሰፊ ምሁራዊ ውይይት ተካሂዷል፡፡ በጥናት መድረኩ ላይ ለኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄን በማስመለስ ታሪካዊ ድል ያስመዘገቡ ያለፈው ትውልድ ምርጥ ተሞክሮ ታሪካዊ ድል እንደነበር ተገልጿል፡፡ በሰላማዊ መንገድ ኤርትራን በፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ጋር…
Read More
በሀሪ ማጓየር ላይ ትችት የሰነዘሩት ጋናዊ የፓርላማ አባል ይቅርታ ጠየቁ፡፡

በሀሪ ማጓየር ላይ ትችት የሰነዘሩት ጋናዊ የፓርላማ አባል ይቅርታ ጠየቁ፡፡

የአፍሪካዊቷ ጋና ህግ አውጪ ምክር ቤት አባል የሆኑት አይዛክ አዶንጎ ከአንድ ዓመት በፊት የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንትን ከማንችስተሩ ተከላካይ ተጫዋች ሀሪ ማጓየር ጋር ተመሳሳይ እንደሆኑ ተናግረው ነበር፡፡ የፓርላማ አባሉ በወቅቱ “የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት እንደ ማጓየር በራሱ ላይ ግብ የሚያስቆጥር፣ ጠንካራ የስራ አጋሮቹን መትቶ የሚጥል እና እንዲቀጡ ለዳኛ አቤት የሚል ነው” ሲሉ ተናግረው ነበር፡፡ ግለሰቡ ይህን ንግግር ያደረጉበት ተንቀሳቃሽ ምስል በተለያዩ ማህበራዊ የትስስር ገጾች ላይ ለብዙ ሰዎች መድረስ ችሏል፡፡ እኝህ የህግ አውጪ አባል “ስለ ማጓየር ከዚህ በፊት የተናገርኩት አስተያየት ስህተት ነበር፣ ማጓየርን ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ ተጫዋቹ አሁን ላይ ምርጥ ተከላካይ መሆኑን አስመስክሯል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ይሁንና ለጋና ምክትል ፕሬዝዳንትን ግን ይቅርታ አልጠይቅም ያሉት…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስራኤል አቋርጦት የነበረውን በረራ እንደሚጀምር ገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስራኤል አቋርጦት የነበረውን በረራ እንደሚጀምር ገለጸ፡፡

ሃማስ በእስራኤል ላይ ድንገተኛ እና ያለተጠበቀ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የተቀሰቀሰው ጦርነት ከተጀመረ 47ኛ ቀኑን ይዟል። ከሁለቱም ወገን 15 ሺህ ገደማ ሰዎች የተገደሉበት ይህ ጦርነት እንዲቆም በርካቶች ሲያሳስቡ ቢቆዩም ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ በጦርነቱ ምክንያት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በርካታ የዓለማችን አየር መንገዶች ወደ እስራኤል ሲያደርጉት የነበረውን በረራ አቋርጠው ቆይተዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከህዳር 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን በረራ ዳግም እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ አየር መንገዱ አክሎም በሳምንት አምስት ቀናት ከአዲስ አበባ-ቴልአቪቭ ከተማ የቀጥታ በረራውን እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡ የደርሶ መልስ ትራንስፖርት አገልግሎቱን በበረራ መስመር ኢት 404 እና 405 አውሮፕላኖቹ  እንደሚሰጥ የገለጸው አየር መንገዱ ሁሉንም የሳምንቱ ቀናት…
Read More
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቡርኪናፋሶ አቻው 3 ለ 0 ተሸነፈ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቡርኪናፋሶ አቻው 3 ለ 0 ተሸነፈ

ዋልያዎቹ በዓለም ዋንጫ የምድብ ማጣርያ ጨዋታ በቡርኪና ፋሶ አቻቸው 3 ለ 0 ተሸንፈዋል፡፡ የቡርኪናፋሶን የማሸነፊያ ግቦች ብላቲ ቱሬ በ69 ኛው፣ በርትራንድ ትራኦሬ በ78ኛው እንዲሁም ዳንጎ ኦታትራ 90ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎም በ2026 ካናዳ ሜክሲኮ እና አሜሪካ በጥምረት ለሚያዘጋጁት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ አንድ የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድቡ 1 ነጥብ በመያዝ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡ ብሔራዊ ቡድኑ በቀጣይ የአለም ዋንጫ የምድቡን ሶስተኛ እና አራተኛ የማጣሪያ ጨዋታዎች ከጊኒ ቢሳኦ እና ጅቡቲ ጋር የሚያደርግ ይሆናል፡፡
Read More
የአሜሪካው ራክሲዮ የቴክኖሎጂ ኩባንያ የዳታ ማዕከሉን በኢትዮጵያ ከፈተ

የአሜሪካው ራክሲዮ የቴክኖሎጂ ኩባንያ የዳታ ማዕከሉን በኢትዮጵያ ከፈተ

የዳታ ማዕከሉ 30 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን በአፍሪካ 2ኛዉን የዳታ ማዕከል በአዲስ አበባ ከፍቷል። በአፍሪካ ገለልተኛ የመረጃ ማዕከል የሆነዉ ራክሲዮ ግሩፕ በኢትዮጵያ 2ኛዉን የዳታ ማዕከል በ30 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወጪ ኢንቨስትመንት በመገንባት አስጀምሯል። ኩባንያው የዳታ ማዕከሉን በአዲስ አበባ በአይሲቲ ፓርክ ውስጥ መክፈቱን የገለጸ ሲሆን የዳታ ፍሰትን ሙሉ በሙሉ በአገር ዉስጥ በማድረግ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ድርጅቶች ለኢንተርኔት የሚያወጡትን ወጪ ለመቀነስ ይረዳል ተብላል። በኢትዮጵያ የተከፈተዉ አዲሱ የደረጃ III የመረጃ ማዕከል 800 ራኮች እና እስከ 3MW የአይቲ ሃይል አለዉ ተብሏል። በ2018 የተቋቋመዉ ራክሲዮ በአፍሪካ የመጀመሪያውን የዳታ ማዕከል በኡጋንዳ እንደከፈተ ገልጿል። ኩባንያው ሁለተኛውን የዳታ ማዕከል በኢትዮጵያ ዛሬ ያስጀመረ ሲሆን እስከ ሚቀጥለው ዓመት ድረስም በኮንጎ  ፣…
Read More