24
Aug
በዘንድሮው ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች ውስጥ 565 ያህሉ አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸው ተገልጻል። ዘንድሮ በ2018 ብሔራዊ ፈተና የተመዘገበው ተማሪ ቁጥር 563,960 ሲሆን 550,210 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል። ከተፈተኑት ውስጥም 12 በመቶ ወይም 70 ሺህ 544 ተማሪዎች ብቻ ወደ ዩንቨርስቲ የሚያስገባቸውን ውጤት አስመዝግበዋል ተብሏል። ከተፈጥሮ ሳይንስ 16.6 በመቶ እንዲሁም ከማህበራዊ ሳንይስ 8.3 በመቶ ያህሉ ማለፋቸውን የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ተናግረዋል። አዲስ አበባ ካስፈትናቸው ተማሪዎች ውስጥ 32.3 በመቶዎቹ ሲያልፉ፣ ሀረሪ 22.67%፣ አፋር 15.6%፣ አማራ 15.56%፣ ድሬዳዋ 11.29፣፣ ትግራይ 11.2%፣ ኦሮሚያ 10.5 በመቶ አሳልፈዋል። ባለፉት ዓመታት ዋነኛ የግጭት እና ጦርነት ቀጠና በሆኑት በአማራ፣ ኦሮሚያ እና ትግራይ ክልል ያለፉ ተማሪዎችን ስንመለከትም በኦሮሚያ…