canada

ካናዳ ዜጎቿ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ አስጠነቀቀች

ካናዳ ዜጎቿ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ አስጠነቀቀች

በካናዳ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አማካኝነት የወጣው ይህ ማስጠንቀቂያ ‹‹ወሳኝ ላልሆነ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ወደ ኢትዮጵያ እንዳትሄዱ› የሚል መልእክት ያለው ሲሆን ለዚህም የሰጠው ምክንያት የእርስ በእርስ ግጭት፣ አመፅ፣ የጦር መሳሪያ ግጭት ወንጀል እና የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት ናቸው። የጉዞ ማስጠንቀቂያው የፀጥታ ሁኔታው ድንገት ሊባባስ እንደሚችል አሳስቦም ይህ ማስጠንቀቂያ አዲስ አበባን እንደማይመለከት አስታውቋል፡፡ ይሁን እንጂ ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ ዜጎቹም ቢሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው ገልፆ በከተማው ውስጥ የወንጀል መጠኑ ከፍተኛ መሆኑንና በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች እየተካሄደ ያለው የትጥቅ ትግል ያለምንም ማስጠንቀቂያ ወደ ከተማው ሊዛመት የሚችልበት እድል እንዳለ አስታውቋል፡፡ ይህ ማስጠንቀቂያ እንዳለው የካናዳ ዜጎች ከአዲስ አበባ ውጪ ወደ አማራ፣ ትግራይና ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልሎች…
Read More
ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ ”ሳምራ” በሚል የሰየመውን የኢትዮጵያ ቡና ለገበያ አቀረበ

ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ ”ሳምራ” በሚል የሰየመውን የኢትዮጵያ ቡና ለገበያ አቀረበ

ከኢትዮጵያዊ ቤተሰቦቹ በካናዳ ተወልዶ ያደገው ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ “ዘ ዊክኤንድ”፤ የእናቱን እና የቤተሰቡን ትውልድ አገር ለማክበር በሚል በእናቱ ሥም የሰየመውን ”ሳምራ” የተሰኘ የኢትዮጵያ ቡና ለአለም ዓቀፍ ገበያ አቀረበ። አቤል ቡናውን ከ“ብሉ ቦትል ኮፊ” ጋር በመተባባር ለሽያጭ ማቅረቡን በትዊተር ገጹ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ ይፋ አድርጓል። አቤል ተስፋዬ እና የሪከርድ ኩባንያው በጋራ በመሆን “ብሉ ቦትል ኮፊ” በሚል ሥም ባቋቋሙት ድርጅት ሥር የኢትዮጵያን ባሕል እና የኢትዮጵያን ቡና በዓለም ደረጃ መሸጥ መጀመራቸውን ገልጿል፡፡ አቤል የ“ሳምራ ቡና” ወደገበያ መግባትን አስመልክቶ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ "የኢትዮጵያ ባህል የማንነቴ ወሳኙ አካል ነው” ያለ ሲሆን፤ ከ‘ብሉ ቦትል ኮፊ’ ጋር በመሆን የኢትዮጵያን ባሕል፣ ወጎች፣ እሴቶች እና ቡና ላይ የዓለም…
Read More