Tourism

ኢትዮጵያ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

በ2015 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የሚኒስቴሩ የኮሙኒኬሽንና የሕዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ አለማየሁ ጌታቸው እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተለይም አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን ከማልማት እንዲሁም ነባሮችን ከማደስ እና ከመጠገን አንጻር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተዋል፡፡ የጮቄ ተራራ እና ወንጪ የኢኮ ቱሪዝም መዳረሻዎች በዓለም ቱሪዝም ድርጅት እውቅና እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉንም አስታውሰዋል። በተለያዩ አካባቢዎች ተጨማሪ የኢኮ ቱሪዝም መዳረሻ ሊሆኑ የሚችሉ ቦታዎችን በጥናት የመለየት እና መረጃ የማሰባሰብ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡ በበጀት ዓመቱም በርካታ ቁጥር ካላቸው የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ነው አቶ አለማየሁ…
Read More
ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከውጭ ጎብኚዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከውጭ ጎብኚዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከውጭ ጎብኚዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 44 ቢሊዮን ብር አግኝታለች። እንዲሁም ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ደግሞ 2 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገልጿል ። የቱሪዝም ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በተያዘው በጀት ዓመት 6 ወራት ውስጥ ኢትዮጵያ በ504,840 በሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ተጎብኝታለች። ከነዚህ ጎብኚዎችም ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን ሚንስቴሩ ጠቅሷል። ቱሪስቶች፤ ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንሶች የተገኙ ተሳታፊዎችና የቢዝነስ ሰዎችም በዚህ ሪፖርት ተካተዋል። በአዲስ አበባ የቱሪስት ቆይታም በአማካይ ከ5 እስከ 6 ቀናት እንደሆነም በሪፖርቱ ተጠቅሷል። ከሀገር ውስጥ ጎብኝዎችም 44 ቢሊዮን ብር መገኘቱ የተገለጸ ሲሆን ይህም ሚኒስቴሩ ካስቀመጠው 32.9 ቢሊዮን ብር እቅድ…
Read More