Tourismethiopia

ኢትዮጵያ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

በ2015 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የሚኒስቴሩ የኮሙኒኬሽንና የሕዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ አለማየሁ ጌታቸው እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተለይም አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን ከማልማት እንዲሁም ነባሮችን ከማደስ እና ከመጠገን አንጻር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተዋል፡፡ የጮቄ ተራራ እና ወንጪ የኢኮ ቱሪዝም መዳረሻዎች በዓለም ቱሪዝም ድርጅት እውቅና እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉንም አስታውሰዋል። በተለያዩ አካባቢዎች ተጨማሪ የኢኮ ቱሪዝም መዳረሻ ሊሆኑ የሚችሉ ቦታዎችን በጥናት የመለየት እና መረጃ የማሰባሰብ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡ በበጀት ዓመቱም በርካታ ቁጥር ካላቸው የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ነው አቶ አለማየሁ…
Read More
የአክሱም ሀውልት ከሁለት ዓመት ጦርነት በኋላ ለጎብኚዎች ክፍት ተደረገ

የአክሱም ሀውልት ከሁለት ዓመት ጦርነት በኋላ ለጎብኚዎች ክፍት ተደረገ

የአክሱም ሀውልት ዳግም ለጎብኚዎች ክፍት መደረጉን በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የአክሱም ከተማ ባህልና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። የጽሕፈት ቤቱ ሀላፊ ገብረመድህን ፍፁም ብርሀን፤ በአክሱም ከተማና አካባቢው የሚገኙ የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ ጥንታዊ ቅርሶች ለቱሪስቶች ክፍት መደረጋቸውን ተናግረዋል። ቅርሶቹ ዳግም ለጎብኚዎች ክፍት እንዲሆኑ ሕብረተሰቡ በጉልበቱ፣ በገንዘቡና በሙያው ያደረገው ተሳትፎ የላቀ እንደነበርም ገልጸዋል። የቱሪዝሙን ዘርፍ ወደነበረበት ለመመለስና ሕብረተሰቡ ለቱሪስቶች የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሳደግ ለፎቶ ግራፍ ባለሙያዎች፣ አስተርጓሚዎች፣ ለባህላዊ ጌጣጌጦችና ቅርፃ ቅርፅ ባለሙያዎች እንዲሁም ለባለ ሆቴሎች ስልጠና መሰጠቱንም አስረድተዋል። በአክሱምና አካባቢው የሚገኙ ቅርሶችና ሙዚየም ለጎብኚዎች ተደራሽ ለማድረግ ከዛሬ ጀምሮ ክፍት መደረጋቸውን ገልጸዋል። በአክሱምና አካባቢው የሚገኙ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ጥንታዊ ቅርሶች ለመጎብኘትና ለማየት በየዓመቱ ከ30 ሺሕ በላይ…
Read More
ኢትዮጵያን የጉዛራ ቤተ መንግሥት በ35 ነጥብ ስምንት ሚሊየን ብር ጥገና ሊደረግለት ነው

ኢትዮጵያን የጉዛራ ቤተ መንግሥት በ35 ነጥብ ስምንት ሚሊየን ብር ጥገና ሊደረግለት ነው

በዓለም ቅርስነት የተመዘገበው በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚገኘው የጉዛራ ቤተመንግሥት ከተደቀነበት የመፍረስ አደጋ ለመታደግ፤ ከፌደራል መንግሥት በተበጀተ 35 ሚሊዮን 800 ሺሕ ብር በጀት የጥገና ሥራው በዛሬው ዕለት እንደሚጀመር ተገልጿል። የጥገና ሥራው በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የጎንደር ዙሪያ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት የቅርስ ጥበቃና ቱሪዝም ልማት ቡድን መሪ ግርማቸው ሙሉጌታ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። ጉዛራ ቤተመንግሥት በጣና ተፋሰስ አካባቢዎች የሚገኝ የመጀመሪያው ቤተመንግሥት እንደሆነ ይነገራል። ጉዛራ ቃሉ የግዕዝ ሲሆን፤ ትርጉሙም ምቹ ማለት ነው። በጎንደር የነገሥታት ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን የጉዛራን ቤተመንግሥት የመሰረቱትም ያሳነፁትም ኢትዮጵያን ከ1556-1589 ድረስ በመሩት በአፄ ሰርፀ ድንግል መሆናቸው በፁሁፍ የሰፈሩ ማስረጃዎች ያሳያሉ። የጉዛራ ቤተመንግሥት ከእንፍራንዝ በስተደቡብ 5 ኪሎሜትር ወጣ ብሎ የተሰራ…
Read More
ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከውጭ ጎብኚዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከውጭ ጎብኚዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከውጭ ጎብኚዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 44 ቢሊዮን ብር አግኝታለች። እንዲሁም ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ደግሞ 2 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገልጿል ። የቱሪዝም ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በተያዘው በጀት ዓመት 6 ወራት ውስጥ ኢትዮጵያ በ504,840 በሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ተጎብኝታለች። ከነዚህ ጎብኚዎችም ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን ሚንስቴሩ ጠቅሷል። ቱሪስቶች፤ ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንሶች የተገኙ ተሳታፊዎችና የቢዝነስ ሰዎችም በዚህ ሪፖርት ተካተዋል። በአዲስ አበባ የቱሪስት ቆይታም በአማካይ ከ5 እስከ 6 ቀናት እንደሆነም በሪፖርቱ ተጠቅሷል። ከሀገር ውስጥ ጎብኝዎችም 44 ቢሊዮን ብር መገኘቱ የተገለጸ ሲሆን ይህም ሚኒስቴሩ ካስቀመጠው 32.9 ቢሊዮን ብር እቅድ…
Read More