ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከውጭ ጎብኚዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከውጭ ጎብኚዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 44 ቢሊዮን ብር አግኝታለች።

እንዲሁም ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ደግሞ 2 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገልጿል ።

የቱሪዝም ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በተያዘው በጀት ዓመት 6 ወራት ውስጥ ኢትዮጵያ በ504,840 በሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ተጎብኝታለች።

ከነዚህ ጎብኚዎችም ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን ሚንስቴሩ ጠቅሷል።

ቱሪስቶች፤ ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንሶች የተገኙ ተሳታፊዎችና የቢዝነስ ሰዎችም በዚህ ሪፖርት ተካተዋል።

በአዲስ አበባ የቱሪስት ቆይታም በአማካይ ከ5 እስከ 6 ቀናት እንደሆነም በሪፖርቱ ተጠቅሷል።

ከሀገር ውስጥ ጎብኝዎችም 44 ቢሊዮን ብር መገኘቱ የተገለጸ ሲሆን ይህም ሚኒስቴሩ ካስቀመጠው 32.9 ቢሊዮን ብር እቅድ በላይ ነው ተብሏል።

ሚኒስቴሩ እየጨመረ የመጣውን የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ለማሳደግ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር “ጉዞ” የተሰኘ የቁጠባ ሂሳብ መዘጋጀቱም ተጠቅሷል።

በዚህ የቁጠባ ሂሳብ ለመጪው ጉዟቸው ለሚቆጥቡ ጎብኚዎች በሚቀጥለው ጉዟቸው ላይ ከሚከፍሉት ክፍያ ከ5 እስከ 7 በመቶ ተመላሽ እንዲያገኙ እየተሰራ ነው ተብሏል።

By New admin

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *