25
Oct
በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ያለው የፀጥታ ችግር በድርድር እንዲፈታ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሳስበዋል። ችግሩን በሐይማኖት አባቶች እና በሽማግሌዎች ብቻ ለመፍታት ከመጣር ይልቅ፣ በድርድር እና በእውነተኛ አካታች ውይይት መፍታት እንደሚገባም የፓርቲዎቹ አመራሮች ጥሪ ማቅረባቸውን አሀዱ ሬዲዮ ዘግቧል። የአንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ሲሳይ ደጉ፤ "መንግሥት እና አማራ ክልል የሚገኙ ታጣቂዎች ዋናው ሀገራዊ ምክክር ከመካሄዱ በፊት ያለው የጸጥታ ችግር በሰላም መፈታት አለባቸው" ብለዋል። አቶ ሲሳይ የፌዴራል መንግሥት "ታጣቂዎች ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመጡ ጥሪ አቅርቤያለሁ" የሚለውን ቃሉን ተግባራዊ እንዲያደርግ፤ ጥረት እየተደረገ ከሆነም መንግሥት ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። ይህንን ሀሳብ የሚጋሩት የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ የፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉጌታ ሐድጉ በበኩላቸው፤…