Agriculture

ከ18 የኢንሹራንስ ኩባንያዎች  አርሶ አደሮችን የሚያገለግሉት 4 ብቻ ናቸው ተባለ

ከ18 የኢንሹራንስ ኩባንያዎች አርሶ አደሮችን የሚያገለግሉት 4 ብቻ ናቸው ተባለ

ኢትዮጵያ ለግብርናው ዘርፍ የምትሰጠው የኢንሹራንስ አገልግሎት ሽፋን 0 ነጥብ 04 በመቶ ብቻ እንደሆነ በግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ የገጠር ፋይናንስ ክፍል የቡድን መሪ የሥራ አስፈፃሚ አባል አቶ ጌታቸው መኮንን፤ ከ80 በመቶ በላይ የግብርና መር ኢኮኖሚ ያላት ኢትዮጵያ በአርሶ አደሮቿ ምርት ላይ ለሚደርስ አደጋ የምትሰጠው የመድኅን ሽፋን ከአንድ በመቶ በታች ነው ብለዋል፡፡ "ኢትዮጵያ ለአርሶ አደሮቿ የምትሰጠው የግብርና መድኅን ሽፋን ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ሲነፃፀር እጅግ አነስተኛ ነው" ያሉት ሥራ አስፈጻሚው፤ "በኢትዮጵያ ከሚንቀሳቀሱ 18 የኢንሹንስ ኩባንያዎች መካከል ለአርሶ አደሮች የኢንሹራንስ አገልግሎት ለመስጠት ፈቃድ አግኝተው በመስራት ላይ የሚገኙት 4 ብቻ ናቸው" ብለዋል። ባለፉት 10 ዓመታት በኢትዮጵያ በተለያዩ አጋር ድርጅቶች የኢንሹራንስ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለው ከ3…
Read More
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በሚሰጠው የብድር ወለድ ላይ ማሻሻያ አደረገ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በሚሰጠው የብድር ወለድ ላይ ማሻሻያ አደረገ

ባንኩ በግብርና ስራዎች ለተሰማሩ ተበዳሪዎች የብድር ወለድ መጠኑን ከ11 በመቶ ወደ 7 በመቶ ዝቅ ማድረጉን አስታውቋል። ባንኩ በኢትዮጵያ የግብርና ስራዎችን ለማበረታታት በሚል ለተበዳሪዎች በሚሰጠው ብድር ላይ ያስከፍል በነበረው ወለድ ምጣኔ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ገልጿል። የብድር ወለድ ቅናሽ የተደረገው ያ ያልታረሰን የመሬት ሀብት ወደ ስራ ለማስገባት፤ ባለሀብቶች፣ አርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የበለጠ እንዲበረታቱ ለማድረግ በማሰብ እንደሆነ አስታውቋል። በዚህም መሰረት በአነስተኛ፣ መካከለኛና የኮርፖሬት ፕሮጀክት ብድር ለሚጠይቁ ይጠበቅ የነበረው የ11.5 በመቶ የማበደሪያ የወለድ ተመን ወደ 7 በመቶ ዝቅ አድርጓል ብሏል። ልማት ባንክ የሀገር ውስጥ ምርቶችን ለማሳደግ እና ከውጭ ተመርተው ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት በሚል የተቋቋመ የመንግስት የልማት ድርጅት…
Read More