earthquake

የከሰም ስኳር ፋብሪካ በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ምክንያት ከ3 ሺህ በላይ ሠራተኞቹን አሰናበተ

የከሰም ስኳር ፋብሪካ በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ምክንያት ከ3 ሺህ በላይ ሠራተኞቹን አሰናበተ

በአፋር ክልል ዱላሳ ወረዳ የሚገኘው ከሰም የስኳር ፋብሪካ፣ በክልሉ እየተከሰተ ባለው ለወራት የቀጠለ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ይፋ ባደረገ በወሩ፣ ከ3,700 በላይ ሠራተኞቹን ከሥራ ማሰናበቱ ታወቀ። በክልሉ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ በመጣው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ምክንያት ተፈናቅለው በካምፕ የተጠለሉ 3,750 ቋሚና ጊዜያዊ የከሰም ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች፣ የካቲት 12 ቀን 2017 ዓ.ም. ባልጠበቁት ሁኔታ ከሥራ ተሰናብተዋል። ከቻይና ልማት ባንክ በተገኘ 123 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተገነባው ከሰም ስኳር ፋብሪካ ከ10 ዓመት በፊት ነበር ስኳር ማምረት የጀመረው፡፡ በዓመት 260 ሺህ ቶን ስኳር የማምረት አቅም የነበረው ይህ ስኳር ፋብሪካ በአዋሽ አካባቢ ባጋጠመው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ምክንያት ስራ አቁሟል፡፡ በ20 ሺህ ሄክታር መሬት…
Read More
በኢትዮጵያ ባጋጠመው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 80 ሺህ ዜጎች እንደሚፈናቀሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ባጋጠመው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 80 ሺህ ዜጎች እንደሚፈናቀሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች እየተደጋገሙ ሲሆን እስካሁን መኖሪያ ቤቶች ላይ የተወሰኑ ጉዳቶችን ከማድረስ የዘለለ ከባድ ጉዳት አላደረሱም፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ30 ጊዜ በላይ በአፋር ክልል አዋሽ ከተማ አቅራቢያ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች ያጋጠሙ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ከ60 ዓመት በኋላ ከፍተኛ የጠባለ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አጋጥሟል፡፡ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ሪፖርት እንደገለጸው ከሆነ በሬክተር ስኬል 5 ነጥብ 8 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አጋጥሟል፡፡ በዚህ አደጋ ምክንያት በአፋር ክልል ባሉ መኖሪያ ቤቶች እና የመንግስት ተቋማት ላይ አነስተኛ ጉዳት ያጋጠመ ሲሆን ንዝረቱ አዲ አበባ ድረስ ተሰምቷል፡፡ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው ማስታወቂያ የርዕደ መሬቱ ማዕከል ከሆኑ 12 ቀበሌዎች 80 ሺህ ዜጎችን ሊፈጠር…
Read More
በኢትዮጵያ ባንድ ቀን ውስጥ ከ14 ጊዜ በላይ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከሰተ

በኢትዮጵያ ባንድ ቀን ውስጥ ከ14 ጊዜ በላይ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከሰተ

በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች እየተደጋገሙ ሲሆን እስካሁን መኖሪያ ቤቶች ላይ የተወሰኑ ጉዳቶችን ከማድረስ የዘለለ ከባድ ጉዳት አላደረሱም፡፡ አደጋው እያጋጠመ ያለው በአፋር ክልል አዋሽ ልዩ ስሙ ፈንታሌ አካባቢ እንደሆነ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ሪፖርት ያስረዳል፡፡ በአዋሽ ፈንታሌ እየተከሰተ ባለዉ ተደጋጋሚ ርዕደ መሬት ምክንያት ነዋሪዎች ከመኖሪያ ቤታቸው እየለቀቁ ሲሆን እስካሁን ከ2,500 በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል፡፡ ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ በተሰማው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች እስካሁን ከፍተኛው 5 በሬክተር ስኬል 5 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ነው። በአደጋው ከ100 በላይ ቤቶች ጉዳት የደረሰባቸዉ ሲሆን፤ 2 ሺሕ 560 ሰዎች መፈናቀላቸውን እና እንሰሳት መሞታቸውን የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ አስተዳደር አቶ አደም ባሂ ተናግረዋል። አስተዳዳሪው አክለውም በቀን ውስጥ እስከ…
Read More