Eurobond

ኢትዮጵያ ስታካሂደው የነበረው የ1 ቢሊዮን ዶላር ቦንድ ዕዳ ድርድር ተቋረጠ

ኢትዮጵያ ስታካሂደው የነበረው የ1 ቢሊዮን ዶላር ቦንድ ዕዳ ድርድር ተቋረጠ

ኢትዮጵያ የ 1 ቢሊዮን ዶላር የቦንድ ዕዳዋን ለማዋቀር ስታደርግ የነበረዉ ድርድር ያለ ስምምነት ተጠናቀቀ። የኢትዮጵያ መንግሥት በ2024 ዓ.ም. ዋናው ዕዳ የሚከፈልበት የአንድ ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ቦንድ ዕዳዋን ለማዋቀር  ያደረገው ወሳኝ ጥረት ከቦንድ ባለቤቶች ተወካዮች ጋር ሲያደርገው የነበረው ድርድር ያለ ስምምነት መጠናቀቁ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ለዚህ ብድር በየዓመቱ 6.625% ወለድ ለመክፈል መስማማቷ ይታወቃል። የገንዘብ ሚኒስትር እንዳስታወቀው በመስከረም 15 እና ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም መካከል የተካሄደው ውይይት በሁለቱ ወገኖች የቀረቡትን የመጨረሻ የዕዳ ማዋቀር ሃሳቦች መካከል ያለውን ልዩነት ማጥበብ አልተቻለም። ሚኒስቴሩ ድርድሩ በዚህ ጊዜ ሳይሳካ ቢቀርም፣ "ሰፊ መሻሻል" መመዝገቡን ገልጾ፣ ውይይቱ ወደፊት እንደሚቀጥል ተስፋውን አጠናክሯል። ሁለቱም ወገኖች ለአዲሱ ቦንድ እትም ዋናውን ዕዳ በ15%…
Read More
ኢትዮጵያ በ1 ቢሊዮን ዩሮቦንድ ዕዳ ዙሪያ አዲስ ውይይት ጀመረች

ኢትዮጵያ በ1 ቢሊዮን ዩሮቦንድ ዕዳ ዙሪያ አዲስ ውይይት ጀመረች

ኢትዮጵያ የ1 ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ዕዳዋን እንደገና ለማዋቀር ከግል ባለቤቶች ጋር ሚስጥራዊ ውይይት ጀምራለች። የኢትዮጵያ መንግስት የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ ዕዳን እንደገና ለማዋቀር (restructure) ከዓለም አቀፍ የቦንድ ባለቤቶች ኮሚቴ ጋር ይፋዊ እና ሚስጥራዊነትን ያካተተ ውይይት መጀመሩን ብሉምበርግ ዘግቧል። ይህ እርምጃ ሀገሪቱ በከባድ የዕዳ ጫናዋን ለማቃለል በምታደርገው ጥረት ውስጥ እንደ ወሳኝ ምዕራፍ ተወስዷል። ውይይቱ "restricted" ተብሎ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህ ማለት በድርድሩ ላይ የሚሳተፉት አበዳሪዎች (የቦንዱ ባለቤቶች) "የምስጢራዊነት ስምምነት" (NDA) መፈረም ነበረባቸው። ይህ ስምምነት የኢትዮጵያ መንግስት ለስምምነቱ መሳካት ወሳኝ የሆኑ ሚስጥራዊ የኢኮኖሚ መረጃዎችን ለአበዳሪዎቹ እንዲያካፍል ያስችለዋል። ስምምነቱን የፈረሙ ባለቤቶች በውይይቱ ወቅት የኢትዮጵያን ቦንድ መሸጥም ሆነ መግዛት አይችሉም። ይህ የውይይት እርምጃ የመጣው ኢትዮጵያ…
Read More