orthodoxchurch

ቤተ ክርስቲያኗ በትግራይ ክልል ያሉ የአራት ሊቀ ጳጳስን ክህነት አነሳች

ቤተ ክርስቲያኗ በትግራይ ክልል ያሉ የአራት ሊቀ ጳጳስን ክህነት አነሳች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትግራይ ክልል የተሰጠው ኤጲስ ቆጵሳት ሹመት ህገወጥ መሆኑን አስታውቃለች። የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ በተፈጠረው ወቅታዊ የዶግማ፣ የቀኖናና የአስተዳደራዊ ጥሰቶችን አስመልክቶ ውሳኔዎች አሳልፌያለሁ ብሏል። ቤተ ክርስቲያኗ አክላም ከፍተኛውን ሐዋርያዊ ተልእኮ እንዲወጡ አደራ በተሰጣቸው ሊቃነ ጳጳሳት በማኅበረሰብ ዕድገትና አስተዳደር ውስጥ ከሕዝብ ጋር በቆመች፣ ከፖለቲካ በጸዳች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ መንፈሳዊና ሕዝባዊት ተቋምነቷን በመካድ ከፍተኛ የሆነ ሕገ ወጥ ድርጊትና ተቋምን የመናድ እንደሁም መዋቅሯን የማፍረስ ተግባር ተከናውኖብኛል ብላለች። ሐምሌ 16 እና 23 ቀን 2015 ዓ/ም በክልል ትግራይ በማእከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም ገዳም ውስጥ የተፈጸመውን ሕገወጥ የሆነ አስነዋሪ፤ የቀኖና ቤተ…
Read More
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትግራይ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትግራይ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀች

ቤተ ክርስቲያኗ ዘጠኝ ኤጲስ ቆጶሳትን እንደምትሾም አስታውቃለች ቤተክርስቲያኗ ባወጣችው መግለጫ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ በተፈጸመው ሲመት በቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ የደረሰውን መከራና ፈተና ለማሳለፍ ሲባል ዶግማዋን፣ ቀኖናዋን እና ትውፊቷን ባስጠበቀ ሁኔታ ችግሩ በውይይት እንዲፈታ ትረት ስታደርግ መቆየቷን ገልጻለች። በዚህ መሰረትም የካቲት 8 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠቅላይ ሚኒስቴር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በተደረሰው ስምምነት መሠረት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ቀኖናዋን ከስምምነቱ ፤ ስምምነቱን ከቀኖናዋ ጋር በማዛመድ በኦሮሚያ እና በደቡብ ክልል ባሉ ክፍት አህጉረ ስብከት ተመድበው የሚያገለግሉ 9 ኤጲስ ቆጶሳት በቀኖና ቤተ ክርስቲያን እንዲሾሙ…
Read More
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን የ23 የቀድሞ አባቶችን ውግዘት አነሳች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን የ23 የቀድሞ አባቶችን ውግዘት አነሳች

ቤተ-ክርስቲያኒቱ ከህግ ውጭ ሲመተ ጵጵስና የሰጡና የተቀበሉ 26 የቀድሞ አባቶችን ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ማውገዟ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የሦስት ጳጳሳትንና የ20 መነኮሳትን ውግዘት አንስቷል። ውግዘቱ የተነሳው ከዛሬ መጋቢት 21፤ 2015 ዓ.ም. ጀምሮ እንደሆነ ምልዓተ ጉባኤው አሳውቋል። ቅዱስ ሲኖዶስ በመግለጫው "ሦስቱም የቀድሞ ሊቃነ ጳጳሳት ማለትም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ እና ብፁዕ አቡነ ዜናማርቆስ ላይ የተላለፈው ውግዘት ከዛሬ መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ተነስቷል" ብሏል፡፡ በቀድሞ የሊቀ ጳጳስነት ማዕረጋቸው እንዲጠሩና ተመድበው ይሰሩበት በነበረው የስራ ኃላፊነታቸው እንዲቀጥሉም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ የየካቲት ስምንቱን ባለ10 ነጥብ ስምምነት እንቀበላለን ብለው ለቅዱስ ሲኖዶስ ደብዳቤ ያስገቡ 20 የቀድሞ አባቶች ውግዘትም…
Read More