ዜና

ለአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ምርጫ ሶስት ዕጩዎች ይፋ ሆኑ

ለአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ምርጫ ሶስት ዕጩዎች ይፋ ሆኑ

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ምርጫ በየአራት ዓመቱ የሚካሄድ ሲሆን ላለፉት ሰባት ዓመታት የህብረቱ ሊቀመንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሃማት ስልጣን ሊጠናቀቅ ጥቂት ወራት ቀርቶታል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ባሳለፍነው ነሀሴ ባወጣው ማስታወቂያ የህብረቱ አባል ሀገራት እጩዎች እንዲመዘገቡ በጠየቀው መሰረት ኬንያ፣ ጅቡቲ እና ማዳጋስካር እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ዕጩ አቅርበው ጸድቆላቸዋል፡፡ ይህን ተከትሎም የኬንያ ፕሬዝዳንት ለመሆን አራት ጊዜ ተወዳድረው የተሸነፉት ራይላ ኦዲንጋ በይፋ የህብረቱ ሊቀመንበር ምርጫ ተወዳዳሪ ከሆኑት መካከል አንዱ ሆነዋል፡፡ የኬንያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም የራይላ ኦዲንጋ ጥያቄን በአዲስ አበባ በይፋ ያስተዋወቀ ሲሆን የምረጡኝ ቅስቀሳውን በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ከኬንያ በተጨማሪም የጅቡቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሀሙድ አሊ የሱፍ እና የቀድሞ የማዳጋስካር ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶ…
Read More
መንግስት ታዳጊዎችን በግዳጅ ለውትድርና እየመለመለ ነው ተባለ

መንግስት ታዳጊዎችን በግዳጅ ለውትድርና እየመለመለ ነው ተባለ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የክልሉ የአስተዳደር እና የጸጥታ አካላት የመከላከያ ሰራዊት አባል ለመሆን የሚፈልጉ ዜጎችን ምልመላ አስመልክቶ ያደረገውን ምርመራ ይፋ አድርጓል፡፡ ከሚሽኑ ምርመራውን በኦሮሚያ ክልል በአዳማ፣ በቢሾፍቱ፣ በጅማ እና በሻሸመኔ ከተሞች የሚገኙ እጩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ማቆያ ስፍራዎችን በመጎብኘት፤ በማቆያ ስፍራዎቹ ውስጥ የሚገኙ ሰዎችን እና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችን በጉዳዩ ዙሪያ ቃለ መጠይቅ ማድረጉን ገልጿል። የኦሮሚያ ክልል አስተዳደርም የመከላከያ ሰራዊት ምልመላ ሂደቱን በመከላከያ ሚኒስቴር መስፈርቶች መሠረት እንዲያከናውን መጠየቁን እንደተረዳ ኮሚሽኑ አስታውቋል። ይሁንና የኦሮሚያ ክልል የአስተዳደር አካላት እና የጸጥታ ኃይሎች አባላት በመከላከያ ሚኒስቴር ከተገለጸው የምልመላ መስፈርት ውጪ ሕፃናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎችን “የመከላከያ ሰራዊትን እንዲቀላቀሉ” በሚል በግዳጅ እንደያዙ…
Read More
ኢትዮጵያ 10 የኢንዱስትሪ ፓርኮቿን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንነት አሳደገች

ኢትዮጵያ 10 የኢንዱስትሪ ፓርኮቿን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንነት አሳደገች

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስፈላጊዉን መስፈርት አሟልተዋል ያላቸዉን 10 ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን እንዲያድጉ መወሰኑ ተገልጿል። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በበኩሉ እንዳስታወቀው በስሩ ከሚያስተዳድራቸው 13 ኢንዱስትሪ ፓርኮችና የድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና መካከል 10ሩ ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ማደጋቸውን አሳዉቋል። አሁን በስራ ላይ ካሉ 13 ኢንዱስትሪ ፓርኮች መካከል ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ያደጉት አዳማ ባህርዳር ፣ ቦሌ ለሚ ፣ ደብረ ብረሃን እና ሀዋሳ ፣ ጅማ ፣ ቂሊንጦ ፣ ኮምቦልቻ ፣ መቀሌ እና ሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መሆናቸው ታዉቋል። በኢትዮጵያ የሚገኙ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ለማሳደግ አዋጅ ቁጥር 1322/2016 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል። ኢንዱስትሪ ፓርኮቹ…
Read More
ዝነኛው የኢትዮጵያ ሙዚቀኛ ማሕሙድ አሕመድ ከመድረክ ሊሰናበት ነው

ዝነኛው የኢትዮጵያ ሙዚቀኛ ማሕሙድ አሕመድ ከመድረክ ሊሰናበት ነው

በኢትዮጵያ ከ50 ዓመታት በላይ ከልጅነቱ አንስቶ የአገራችንን ሙዚቃ በተለያዩ የአገራችን ቋንቋዎች በመዝፈን፣ የአገራችንን ሙዚቃ ከአገር አልፎ በአለም አቀፍ ደረጃ እንዲደመጡ ያደረገው ጋሽ ማህሙድ አህመድ ማይኩን ሊሰቅል መሆኑ ተገልጿል፡፡ ማህሙድ ለኢትዮጵያ የሙዚቃ ዕድገት ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ የጎንደር ዩኒቨርስቲ የክቡር ዶክተር ማዕረግን መስጠቱ የሚታወስ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የሙዚቃ ዘርፍ ዝነኛ  የሆነውን የሙዚቃ አባት ከሙዚቃ አለም የመሰናበቻ ፕሮግራም በአዲ አበባ እና በአሜሪካ እንደሚዘጋጅ ተገልጿል፡፡ የመሰናበቻ ሙዚቃ ፕሮግራም ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲ አበባ ሚለኒየም አዳራሽ የድምጻዊ ማሕሙድ አሕመድ የመጨረሻ የህይወት ዘመን ስንብት ደማቅ ኮንሰርት እንደሚዘጋጅ ተነግሯል ፡፡ በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይም የክቡር ዶ/ር አርቲስት ማሕሙድ አሕመድ የሙዚቃ ሕይወት ላይ የተዘጋጀ መፅሀፍ እንደሚመረቅም ተገልጿል፡፡…
Read More
ብናልፍ አንዱዓለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ተሾሙ

ብናልፍ አንዱዓለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ተሾሙ

የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብናልፍ አንዱዓለም ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው መሾማቸውን የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት ስለሺ በቀለ ባሳለፍነው ግንቦት ወር ላይ መልቀቂያ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡ አምባሳደር ስለሺ በቀለ  በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደርነት ሹመታቸው መልቀቂያ ካስገቡ በኋላ በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት ሌንጮ ባቲ ይተኳቸዋል ተብሎ ተጠብቆ ነበር፡፡ ይሁንና አሜሪካ የአምባሳደር ሌኝጮን ሹመት መቃወሟን ተከትሎ ብናልፍ አንዷለም በዋሸንግተን የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ተሹመዋል፡፡ የቀድሞው የአርባምንጭ ዩንቨርሲቲ መምህር ስለሺ በቀለ በአምባሳደርነት ከመሾማቸው በፊት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሆነው ከአምስት ዓመት በላይ አገልግለዋል፡፡ አምባሳደር ሽለሺ በታለቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ለዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ቃለ መጠይቅ በመስጠት የሚታወቁ ሲሆን በኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና…
Read More
28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ተጭበርበሩ

28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ተጭበርበሩ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ የገንዘብ ደህንነት ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የባንኩ ሪፖርት እስከ ሰኔ 2024 ድረስ ያሉ የገንዘብ እንቅስቀሴዎች ዙሪያ ትኩረቱን አድርጓል፡፡ ባንኩ በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው 28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በአጭበርባሪዎች ገንዘባቸውን አጥተዋል ብሏል፡፡ የማጭበርበር ድርጊቶቹ የተፈጸሙት በሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶች፣ በተሰረቁ የኤትኤም ማሽኖች፣ በሐሰተኛ ቼኮች፣ በሐሰተኛ የስልክ መልዕክት እና ተያያዥ መንገዶች አማካኝነት ነው፡፡ በዚህ ዓመት ባንኮች ያጡት ገንዘብ ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ300 ሚሊዮን ብር ጭማሪ እንዳሳየም በሪፖርቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡ በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ካሉ 31 ባንኮች ውስጥ 28ቱ ሲጭበረበሩ የቀሪዎቹ ሶስት ባንኮች ማንነት ግን በሪፖርቱ ላይ አልተጠቀሰም፡፡ ባንኮች ከአነስተኛ የብድር እና ቁጠባ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ብድሮችን እየሰጡ…
Read More
ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ለነበራት ወዳጅነት መበላሸት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ተጠያቂ አደረገች

ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ለነበራት ወዳጅነት መበላሸት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ተጠያቂ አደረገች

ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር የነበራት ግንኙነት የተበላሸው በጠቅላይ ሚኒስር አብይ አህመድ አማካኝነት ነው ብላለች፡፡ በኤርትራ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት እንደ ቀድሞው አለመሆኑን በደቡብ ሱዳን የኤርትራ አምባሳደር የሆኑት ዮሃንስ ተክለሚካኤል ተናግረዋል። አምባሳደሩ ይህንን የተናገሩት ባልተለመደ ሁኔታ በብሪታኒያ የኤርትራ ኤምባሲ የዩቲዩብ ቻናል ላይ በሰጡት ቃለ ምልልስ ሲሆን፤ ቪዲዮው ይፋ ከተደረገ ከሰዓታት በኋላ እንዲነሳ መደረጉን ቢቢሲ ዘግቧል። ተሻሽሎ የነበረው የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት፤ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓት መካከል የፕሪቶሪያ ስምምነት ከተፈረመ በኋላ በይፋ የተባለ ነገር ባይኖርም የአገራቱ ግንኙነት ተቀዛቅዟል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ እና የስልክ ግንኙነት መቋረጥ ግንኙነቱ ስለመሻከሩ ማሳያ መሆኑ በተደጋጋሚ ሲጠቀስ ቆይቷል። በደቡብ ሱዳን የኤርትራ አምባሳደር ዮሃንስ ተክለሚካኤል ‘ኤርትራ ኤምባሲ ሚዲያ’ (Eritrea…
Read More
ኢትዮጵያ 251 ሚሊዮን ዶላር ብድር ከአይኤምኤፍ አገኘች

ኢትዮጵያ 251 ሚሊዮን ዶላር ብድር ከአይኤምኤፍ አገኘች

ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ 251 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ ብድር እንደሚለቅ አስታውቋል፡፡ ተቋሙ እንዳስታወቀው ብድሩን ለመልቀቅ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ከስምምነት ላይ ደርሷል። ድርጅቱ ብድሩን ለማጽደቅ የተስማማው፣ የድርጅቱ የባለሙያዎች ቡድን ከኅዳር 3 እስከ 17 በአዲስ አበባ ተገኝቶ ኹለተኛውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ግምገማ ማድረጉን ተከትሎ ነው። የድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ፣ የብድር መልቀቅ ስምምነቱን በቀጣይ ሳምንታት ውስጥ እንደሚያጸድቀውና ወደፊት የኢኮኖሚ ማሻሻያ ግምገማዎች በየስድስት ወሩ እንደሚካሄዱ ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ገልጿል። የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደተቀረፈና በመደበኛውና በትይዩ የውጭ ሀገራት መገበያያ ምንዛሬዎች መካከል ያለው ልዩነት ከ10 በመቶ በታች መውረዱን የጠቀሰው ድርጅቱ፣ መንግሥት ጥብቅ የገንዘብና ፊስካል ፖሊስ እንዲቀጥል አሳስቧል። ኢትዮጵያ ካሳለፍነው ሐምሌ ወር ጀምሮ በአይኤምኤፍ እና…
Read More
በአማራ ክልል ከ7000 በላይ እስረኞች ከማረሚያ ቤት አምልጠዋል ተባለ

በአማራ ክልል ከ7000 በላይ እስረኞች ከማረሚያ ቤት አምልጠዋል ተባለ

አማራ ክልል ዉስጥ እየተደረገ ባለ ውጊያ ምክንያት ከ 7000 በላይ እስረኞች ከማረሚያ ቤት አምልጠዋል ተብሏል። ከአመለጡት መካከል አንዳንዶቹ በተጠቂዎች መገደላቸዉ ሲገለፅ ሌሎቹ ደግሞ ከሳሾቻቸዉ ላይ ጉዳት ማድረሳቸዉ ተነግሯል። የአማራ ክልል ምክር ቤት እንዳስታወቀው በክልሉ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ከአሥር ማረሚያ ቤቶች ሰባት ሺሕ ታራሚዎች መበተናቸውን ገልጿል፡፡ በምክር ቤቱ መደበኛ ጉባዔ ላይ እንደተገለጸው በክልሉ በወቅታዊ የፀጥታ ችግር ምክንያት ከተበተኑበት ተይዘው የተመለሱት በጣም አነስተኛ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም በክልሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ ባለው ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር ላይ የሚደረገው ቁጥጥር በታቀደው ልክ አለመሳካቱን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ በሚታየው የፀጥታ ችግር የሕዝቡ ነፃ እንቅስቃሴ በሰፊው የተገደበ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን ግድያ፣ ዝርፊያ፣ ዕገታ፣ የዜጎች እንግልት፣ ከእሴትና…
Read More
አምንስቲ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ ያስተላለፈችውን እገዳ ተቃወመ

አምንስቲ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ ያስተላለፈችውን እገዳ ተቃወመ

የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረስበ ድርጅቶች ባለስልጣን በሲቪል ማህበረሰብ ስራዎች ዙሪያ የተሰማሩ ድርጅቶችን ማሸጉ ይታወሳል፡፡ ከታገዱት ድርጅቶች መካከልም “የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል” (CARD) “ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” (AHRE) እና ሌሎችም ይገኙበታል። ባለሥልጣኑ ለድርጅቶቹን ያገደው በፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ ጣልቃ ገብተዋል በሚል ነበር፡፡ አለም አቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተቆርቋሪው አምነስቲ ኢንተርናሽናል የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በሦስት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ የጣለውን እገዳ አውግዟል፡፡ የመብቶች እና የዲሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ)፣ ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች በኢትዮጵያ እና የሕግ ባለሙያዎች ለሰብዓዊ መብቶች የተሰኙት ድርጅቶች ላይ የተጣለው እገዳ በሲቪል ማኅበረሰቡ ምኅዳር ላይ የተቃጣው አፈና እየጨመረ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ሲልም አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ ላይ ጠቅሷል። የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምሥራቅ እና ደቡባዊ…
Read More