Music

ዝነኛው የኢትዮጵያ ሙዚቀኛ ማሕሙድ አሕመድ ከመድረክ ሊሰናበት ነው

ዝነኛው የኢትዮጵያ ሙዚቀኛ ማሕሙድ አሕመድ ከመድረክ ሊሰናበት ነው

በኢትዮጵያ ከ50 ዓመታት በላይ ከልጅነቱ አንስቶ የአገራችንን ሙዚቃ በተለያዩ የአገራችን ቋንቋዎች በመዝፈን፣ የአገራችንን ሙዚቃ ከአገር አልፎ በአለም አቀፍ ደረጃ እንዲደመጡ ያደረገው ጋሽ ማህሙድ አህመድ ማይኩን ሊሰቅል መሆኑ ተገልጿል፡፡ ማህሙድ ለኢትዮጵያ የሙዚቃ ዕድገት ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ የጎንደር ዩኒቨርስቲ የክቡር ዶክተር ማዕረግን መስጠቱ የሚታወስ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የሙዚቃ ዘርፍ ዝነኛ  የሆነውን የሙዚቃ አባት ከሙዚቃ አለም የመሰናበቻ ፕሮግራም በአዲ አበባ እና በአሜሪካ እንደሚዘጋጅ ተገልጿል፡፡ የመሰናበቻ ሙዚቃ ፕሮግራም ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲ አበባ ሚለኒየም አዳራሽ የድምጻዊ ማሕሙድ አሕመድ የመጨረሻ የህይወት ዘመን ስንብት ደማቅ ኮንሰርት እንደሚዘጋጅ ተነግሯል ፡፡ በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይም የክቡር ዶ/ር አርቲስት ማሕሙድ አሕመድ የሙዚቃ ሕይወት ላይ የተዘጋጀ መፅሀፍ እንደሚመረቅም ተገልጿል፡፡…
Read More
አርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት እንዲሰጣት ተወሰነ

አርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት እንዲሰጣት ተወሰነ

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለአርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት ሊሰጣት መወሰኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ሐምሌ 13/2015 እንደሚያስመርቅ የገለጹት ፕሬዘዳንቱ፤ በዕለቱ ለተወዳጇ አርቲስት እጅጋየው ሽባባው(ጂጂ) የክብር ዶክትሬት ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ድምፃዊት፣ ገጣሚ፣ የዜማ ደራሲ እና ተዋናይት የሆነችው ሁለገቧ አርቲስት ጂጂ፣ የአገሯን ባህልና ሙዚቃ ለዓለም በማስተዋወቅ እንዲሁም በኪነጥበብ የአዊን ህዝብ ቋንቋ እና ባህል በማሳደግ ላበረከተችው አስተዋፅኦ የክብር ዶክትሬቱ እንደሚበረከትላት ነው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት መግለጻቸውን ከዩንቨርስቲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ለጂጂ የሚሰጠውን የክብር ዶክትሬት እና የተማሪዎቹን የምርቃት ሥነስርዓት በማስመልከት ረቡዕ ማለትም ሐምሌ 12/2015 ከቀኑ 8:00 ሰዓት ለመገናኛ ብዙሀን ዝርዝር መግለጫ እንደሚሰጥም ፕሬዘዳንቱ ገልጸዋል። ከሰሞኑ ለ15ተኛ ጊዜ በተካሄደዉ የአማራ…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም እና ሰዋሰው መተግበሪያ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

ኢትዮ ቴሌኮም እና ሰዋሰው መተግበሪያ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

በእለቱ አብነት አጎናፍርን ጨምሮ የሁለት አርቲስቶች የአልበም ምርቃት፣ የክብር ስጦና እና የፊርማ ስነ ስርአትም ተከናውኗል። ሀገር በቀሉ የሙዚቃ አገልግሎት ሰጪው “ሰወሰው” መተግበሪያ ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል። የስምምነት ፊርማው በሰዋሰው መተግበሪያ እና በሰዋሰው ዩትዩብ ቻናል በኩል የሚሰራጩ የኪነ-ጥበብ ሥራዎችን የቅጂ መብት ለማስከበር ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሏል ። ይህ ስምምነት የኪነ-ጥበብ ስራዎቹ ተደራሽነት ላይም ትርጉም ያለው ለውጥ እንደሚፈጥር ተገልጿል። የመዝናኛውን ኢንዱስትሪ ዲጅታላይዝ በማድረግ በኩል አሻራውን በማሳረፍ ላይ የሚገኘው ሰዋሰው ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በገባው ስምምነት ከነበሩት የክፍያ አማራጮች በተጨማሪ ወደ 9107 አጭር ቁጥር A ወይም B ብሎ በመላክ እለታዊ እና ሳምንታዊ የክፍያ የደንበኝነት ጥቅሎችን በመግዛት ደንበኞች የሚፈልጉትን ሙዚቃ እንዲያገኙ ያስችላል።…
Read More