Injibara

አርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት እንዲሰጣት ተወሰነ

አርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት እንዲሰጣት ተወሰነ

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለአርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት ሊሰጣት መወሰኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ሐምሌ 13/2015 እንደሚያስመርቅ የገለጹት ፕሬዘዳንቱ፤ በዕለቱ ለተወዳጇ አርቲስት እጅጋየው ሽባባው(ጂጂ) የክብር ዶክትሬት ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ድምፃዊት፣ ገጣሚ፣ የዜማ ደራሲ እና ተዋናይት የሆነችው ሁለገቧ አርቲስት ጂጂ፣ የአገሯን ባህልና ሙዚቃ ለዓለም በማስተዋወቅ እንዲሁም በኪነጥበብ የአዊን ህዝብ ቋንቋ እና ባህል በማሳደግ ላበረከተችው አስተዋፅኦ የክብር ዶክትሬቱ እንደሚበረከትላት ነው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት መግለጻቸውን ከዩንቨርስቲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ለጂጂ የሚሰጠውን የክብር ዶክትሬት እና የተማሪዎቹን የምርቃት ሥነስርዓት በማስመልከት ረቡዕ ማለትም ሐምሌ 12/2015 ከቀኑ 8:00 ሰዓት ለመገናኛ ብዙሀን ዝርዝር መግለጫ እንደሚሰጥም ፕሬዘዳንቱ ገልጸዋል። ከሰሞኑ ለ15ተኛ ጊዜ በተካሄደዉ የአማራ…
Read More