amnestyinternational

አምንስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ ላይ ዓለም አቀፍ ጫና እንዲደረግ ጠየቀ

አምንስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ ላይ ዓለም አቀፍ ጫና እንዲደረግ ጠየቀ

አምነስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ አማራ ክልል እየተፈጸመ ነው ያለውን የጅምላ እስራት ለማስቆም አስቸኳይ አለም አቀፍ እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አቅርቧል። ድርጅቱ የሀገሪቱ መንግስት በክልሉ ሰፊ የእስር ዘመቻ ከጀመረበት መስከረም 2024 ጀምሮ አራት ወራት መቆጠራቸውን አመላክቷል፡፡ አምነስቲ ባወጣው መግለጫ እ.ኤ.አ ሴፕቴምበር 28 ቀን 2024 የኢትዮጵያ ፌዴራል እና የአማራ ክልል የጸጥታ ሃይሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦችን ወደ አራት የጅምላ እስር ቤቶች በማጓጓዝ በክልሉ ውስጥ ማሰራቸውን ገልጿል። እስር ከተፈጸመባቸው መካከል ዳኞች፣ አቃቤ ህጎች፣ ፖለቲከኞች እና ምሁራንን ጨምሮ የፍትህ አካላት ይገኙበታል ተብሏል። የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ቀጠና ዳይሬክተር ቲጌሬ ቻጉታህ የአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለጉዳዩ የሰጠውን ትኩረት ማነስ ተችተዋል፡፡ ዳይሬክተሩ "በአማራ ክልል በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በዘፈቀደ…
Read More
አምንስቲ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ ያስተላለፈችውን እገዳ ተቃወመ

አምንስቲ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ ያስተላለፈችውን እገዳ ተቃወመ

የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረስበ ድርጅቶች ባለስልጣን በሲቪል ማህበረሰብ ስራዎች ዙሪያ የተሰማሩ ድርጅቶችን ማሸጉ ይታወሳል፡፡ ከታገዱት ድርጅቶች መካከልም “የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል” (CARD) “ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” (AHRE) እና ሌሎችም ይገኙበታል። ባለሥልጣኑ ለድርጅቶቹን ያገደው በፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ ጣልቃ ገብተዋል በሚል ነበር፡፡ አለም አቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተቆርቋሪው አምነስቲ ኢንተርናሽናል የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በሦስት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ የጣለውን እገዳ አውግዟል፡፡ የመብቶች እና የዲሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ)፣ ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች በኢትዮጵያ እና የሕግ ባለሙያዎች ለሰብዓዊ መብቶች የተሰኙት ድርጅቶች ላይ የተጣለው እገዳ በሲቪል ማኅበረሰቡ ምኅዳር ላይ የተቃጣው አፈና እየጨመረ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ሲልም አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ ላይ ጠቅሷል። የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምሥራቅ እና ደቡባዊ…
Read More
በአማራ ክልል ከተሞች ሰዎች በዘመቻ እየታሰሩ መሆኑ ተገለጸ

በአማራ ክልል ከተሞች ሰዎች በዘመቻ እየታሰሩ መሆኑ ተገለጸ

ዋና መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገው አምንስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ በተለይም በአማራ ክልል ዋና ዋና ከተሞች አዲስ እስር እየተካሄደ እንደሆነ አስታውቋል፡፡ ከመስከረም 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የመንገስት የጸጥታ ሀይሎች ዜጎችን ከህግ ውጪ እየያዙ እያሰሩ መሆኑንም ተቋሙ በሪፖርቱ ለይ ጠቅሷል፡፡ በአምንስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ዳይሬክተር ትግሬ ቻጉታህ እንዳሉት “የኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ንጹሃንን ከህግ ውጪ በዘመቻ ማሰር መጀመራቸው መንግስት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ፍላጎት እንደሌለው ማሳያ ነው” ብለዋል፡፡ ተቋሙ የአይን እማኞችን ጠቅሶ ባወጣው በዚህ ሪፖርቱ ላይ እንደገለጸው ለእስር የተዳረጉ ንጹሃን ህጉ በሚፈቅደው መሰረት በ48 ሰዓት ውስጥ ወደ ፍርድ ቤት እየቀረቡ አለመሆኑንም አስታውቋል፡፡ መንግስት ጀመረው በተባለው የዘመቻ እስር በክልሉ ባሉ ከተሞች የሚገኙ መምህራን እና…
Read More