ዜና

የፌደራል መንግስት 582 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ዓመታዊ በጀት አስጸደቀ

የፌደራል መንግስት 582 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ዓመታዊ በጀት አስጸደቀ

የዘንድሮ ዓመታዊ በጀት ወደ 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር አድጓል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መንግሥት ያቀረበው ተጨማሪ በጀት የተጋነነ ነው ሲሉ ወቅሰዋል፡፡ የፌደራል መንግስት ከስድስት ወር በፊት ለተያዘው በጀት ዓመት 970 ቢሊዮን ብር ዓመታዊ በጀት አጸድቆ ነበር፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የፌዴራል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት ተጨማሪ በጀት እንዲጸድቅለት በቀረበለት ጥያቄ ዙሪያ መክረዋል፡፡ ተጨማሪ በጀቱ ለዕዳ ክፍያ፣  ለማህበራዊ ድጋፍ፣ ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስተካከያ እንዲሆን መታሰቡን  በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መንግስት ተጠሪ ሚኒስትሩ ተስፋዬ ቤልጂጌ ተናግረዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት መንግስት ያቀረበው ተጨማሪ በጀት የተጋነነ ነው ሲሉ ተቃውሞ ቅርበዋል፡፡ ይሁንና ከ2017 አስከ 2021 ድረስ የተነደፈውን የማክሮ ኢኮኖሚ እና የፊስካል ፖሊሲ ማዕቀፍ…
Read More
ኢትዮጵያ የእስላማዊ አገራት ትብብር ድርጅትን ልትቀላቀል ነው ተባለ

ኢትዮጵያ የእስላማዊ አገራት ትብብር ድርጅትን ልትቀላቀል ነው ተባለ

ኢትዮጵያ ዋና መቀመጫውን ጅዳ ሳውዲ አረቢያ ካደረገው ዓለም አቀፉ የእስላማዊ ሀገራት ትብብር ድርጅት አባል ለመሆን እንቅስቃሴ መጀመሯ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ ከድርጅቱ አባል ሀገራት መካከል የተወሰኑትን ድጋፍ አግኝታለችም ተብሏል፡፡ የኦርጋናይዜሽን ኦፍ እስላሚክ ኮፕሬሽን  ወይም የእስላማዊ አገራት ትብብር ድርጅት 57 ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የዚህ ድርጅት አባል ለመኾን ከድርጅቱ ጋር ንግግር መጀመሯን ዋዜማ ዘግቧል። በቻዳዊው ሂሴን ብራሂም ታሃ የሚመራው ድርጅቱ በዓለም ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቀጥሎ በአባላት ብዛት ትልቁ የበይነ መንግሥታት ማኅበር ነው። ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመኾን ንግግር የጀመረችው፣ ከድርጅቱ በቀረበላት ግብዣ መሠረት እንደኾነም ተገልጿል። ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመኾን በጀመረችው እንቅስቃሴ የቱርክን፣ ፓኪስታንን እና የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶችን ድጋፍ አግኝታለች ተብሏል። ከአፍሪካ ጅቡቲ፣…
Read More
ኢትዮጵያ የፕላስቲክ ምርቶች መጠቀምን የሚከለክል ህግ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ የፕላስቲክ ምርቶች መጠቀምን የሚከለክል ህግ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ ለአንድ ጊዜ ግልጋሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶች ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የሚከለክል ህግ አዘጋጀች፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፕላስቲክ ምርቶች አጠቃቀም ላይ ገደብ የሚጥል ረቂ ህግ ላይ ተወያይቷል፡፡ ምክር ቤቱ ባሳለፍነው ሳምንት ለአንድ ጊዜ ግልጋሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የሚከለክል ረቂቅ አዋጅን አዘጋጅቷል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ለዝርዝር እይታ እና ተጨማሪ ግብዓት ታክሎበት እንዲጸድቅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመርቷል። ረቂቅ አዋጁ የሀገሪቱን የደረቅ ቆሻሻ አሰባሰብ፣ ማጓጓዝ፣ ክምችት፣ መልሶ አጠቃቀም፣ መልሶ ኡደት እና አወጋገድ ሥርዓት ማስያዝ ላይ ያተኮረ እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሌሊሴ ነሜ በበኩላቸው ለሀገሪቱ ፓርላማ የተመራው ይህ ረቂቅ አዋጅ፤…
Read More
መንግሥት ሁለት የሰብአዊ መብት ድርጅቶችን አገደ

መንግሥት ሁለት የሰብአዊ መብት ድርጅቶችን አገደ

የሲቪል ማህበረስበ ድርጅቶች ባለስልጣን በሰብአዊ መብት ሥራዎች ታዋቂ የሆኑ ድርጅቶችን እንዳሸገ ተገልጿል፡፡ ከታገዱት ድርጅቶች መካከልም “የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል” (CARD) እና “ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” (AHRE) ይገኙበታል። ባለሥልጣኑ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ እና በዚህ ሳምንት ለድርጅቶቹ በተናጠል በላከው ደብዳቤ፣ ድርጅቶቹ ከማንኛውም እንቅስቃሴ መታገዳቸውን አስታውቋል ሲል ዋዜማ ሬዲዮ ዘግቧል። ለእገዳው የሰጠው ምክንያት “ከፖለቲካ ገለልተኛ ሆኖ መሥራት ሲገባው ከዓላማው ውጭ በመንቀሳቀስ የአገርና የህዝብ ጥቅምን የሚጎዱ ተግባራት ላይ በመሰማራቱ ከባድ የህግ ጥሰት መፈጸሙን ማረጋገጥ ተችሏል” የሚል ነው። ከሁለቱ የሰብዓዊ ድርጅቶች በተጨማሪ ሌሎችም እንደታገዱ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡ ይህ እርምጃ መንግሥት በሰብአዊ መብት ጉዳዮች ላይ በሚሠሩ ድርጅቶች ላይ ሲያደረግ የቆየው ጫና የመጨረሻ ከፍታ ነው ሲሉ…
Read More
75 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው ሊመለሱ ነው ተባለ

75 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው ሊመለሱ ነው ተባለ

የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን እንዳስታወቀው በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ተሳትፎ ከነበራቸው 274 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው እንደሚመልስ አስታውቋል፡፡ ከዚህ ውስጥም በመጀመሪያው ምዕራፍ 75ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞቢላይዝ የማድረግ ስራውን በነገው እለት በይፋ እንደሚጀመር ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ ኮሚሽኑ ፕሮግራምና ፕሮጀክቶች በመቅረጽ ከሰባት ክልሎች ከ371 ሺህ በላይ የቀድሞ ተዋጊዎችን ከ760 ሚሊየን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ በሁለት ዓመታት ውስጥ የዲሞቢላይዜሽንና መልሶ ማቋቋም ስራውን ለመጨረስ የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል። ህዳር 12 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮም ለመጀመሪያው ዙር ተዋጊዎች ብተና ማስፈጸሚያ ሀብት መንግስትና ከለጋሾች ማግኘት ተችሏል ተብሏል፡፡ መንግስት ኮሚሽኑ ስራ ሲጀምር 1 ቢሊዮን ብር የተለገሰ ሲሆን በተጨማሪም ከ7 ሀገራት 60 ሚሊየን ዶላር መገኘቱ ተገልጿል። በድጋፍ የአውሮፓ…
Read More
አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ የሮጠበት ማልያ በ2400 ዶላር ተሸጠ

አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ የሮጠበት ማልያ በ2400 ዶላር ተሸጠ

በበርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ስኬታማ አትሌት የሆነው ሀይሌ ገብረስላሴ የሮጠበት አንድ ማልያ በ2 ሺህ 400 ዶላር ተሸጧል፡፡ በአዲስ አበባ በተካሄደ በዚህ ጨረታ ላይ የቀረበው ይህ ማልያ አትሌት ሀይሌ በ1992 በደቡብ ኮሪያ ሴኡል ከተማ በተካሄደው የ10 ሺህ ሜትር ውድድርን ያሸነፈበት ማልያ ነበር፡፡ ይህ ውድድር ለአትሌት ሀይሌ ገብረ ስላሴ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የጀመረበት ወቅት እንደነበርም ተገልጿል፡፡ የታላቁ ሩጫ መስራች እና ባለቤት አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ ለጨረታ ቀርቦ 2 ሺሕ 400 ዶላር የተሸጠው ማልያ የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን ለማጠናከር ይውላልም ተብሏል፡፡ በጨረታው የታላቁ ሩጫ ባዘጋጀው የእራት ግብዣ ፕሮግራም ላይ የኃይሌ ገ/ሥላሴ የሮጠበት ማልያ፤ በእንግሊዛዊ ተጋባዥ እንግዳ አሸንፏል። ይህንን የማልያ ጨረታ እንግሊዛዊ ዜግነት ያለው…
Read More
ኢትዮጵያ በሶስት ወራት ውስጥ ከ87 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ውጭ ሀገራት መላኳ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በሶስት ወራት ውስጥ ከ87 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ውጭ ሀገራት መላኳ ተገለጸ

የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል የሶስት ወራት እቅድ አፈጻጸማቸውን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበዋል፡፡ ሚኒስትሯ በዚህ ወቅት እንደገለጹት ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ 140 ሺህ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ ለመላክ ታቅዶ ነበር ብለዋል፡፡ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በዘንድሮ በጀት ዓመት 700 ሺህ ኢትዮጵያውያንን ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ ለመላክ እቅድ እንደነበረውም ሚኒስትሯ አክለዋል፡፡ ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት 332 ሺህ ኢትዮጵያዊያን ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ መላካቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች የተላከባቸው ሀገራት ስድስት የመካከለኛው ምስራቅ እና ሁለት የአውሮፓ ሀገራት ናቸው።  ሀገራቱ “የሰለጠኑ” እና “በከፊል የሰለጠኑ” ሰራተኞችን ከኢትዮጵያ እንደሚፈልጉ የጠቆሙት ሙፈሪያት፤ በጤና፣ በምህንድስና፣ በአርክቴክቸር፣ በሆቴል እና መስተንግዶ ዘርፎች፣ በኤሌክትሪክ እና ቧንቧ ስራዎች እንደዚሁም…
Read More
ኢህአፓ መንግስት በሚፈጽማቸው የድሮን ጥቃቶች ሰላማዊ ዜጎችን እየገደለ ነው ሲል ከሰሰ

ኢህአፓ መንግስት በሚፈጽማቸው የድሮን ጥቃቶች ሰላማዊ ዜጎችን እየገደለ ነው ሲል ከሰሰ

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ “የዜጎችን ህይወት የመጠበቅ ሃላፊነት ያለበት መንግሥት ቢሆንም በሚያሰማራቸው የጸጥታ ሃይሎችና የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ጭምር የዜጎች ህይወት በበርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች እንደቅጠል እያረገፈ ይገኛል” ብሏል፡፡ ኢሕአፓ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ህገመንግሥቱን የመንግሥት አካላት ራሳቸው ካላከበሩት እንዴት ሊያስከብሩት ይችላሉ “በንጹሀን ዜጎች ላይ የሚደረጉት ግድያዎች ይቁሙ” ሲል አሳስቧል፡፡ እንዲሁም የተለያዩ የመንግስት መገናኛ ብዙሀን ከመዘገብ ቢቆጠቡም በውጪ የመገናኛ ብዙሀን ጭምር ጥቃቱ መፈጸሙን እየገለጹ መሆኑን እና ፓርቲውም አጣርቻለሁ ያለውን በየክልሉ የደረሱትን ጥቃቶች አስታውቋል፡፡ ፓርቲው አጣርቻለው ባለው መሰረት ኦሮሚያ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱ ጥቃቶች የሟቾችን ቁጥር እያሻቀበ መሆኑን እና ጥቃት ከተፈጸመባቸው ውስጥም ነፍሰጡሮች፣ የጤና ባለሙያዎች እና በትምህርት ቤት ውስጥ የነበሩ ተማሪዎች እንደሚገኙበት…
Read More
ኢሰማኮ ለሰራተኞች የሥራ ግብር እንዲቀነስ ጠየቀ

ኢሰማኮ ለሰራተኞች የሥራ ግብር እንዲቀነስ ጠየቀ

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሣሁን ፎሎ እንዳሉት በቋሚ ደመወዝ ለሚተዳደሩ ሰራተኞች የሥራ ግብር መቀነስን ጨምሮ ሌሎች የማሻሻያ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድን በደብዳቤ መጠየቃቸውን ተናግረዋል። የኮንፌደሬሽኑ ፕሬዘዳንት አቶ ካሣሁን ፎሎ እንደገለጹት ከብር የመግዛት አቅም መዳከም ጋር ተያይዞ ቋሚ ደመወዝ የሚያገኙ ሰራተኞች ለከፍተኛ የኑሮ ውድነት መዳረጋቸውን ገልጸዋል። "በተለይም ዝቅተኛ ገቢ የሚያገኘው ሰራተኛ ቀን ቀን እየሠራ ማታ ማታ ሆቴሎች ላይ ፍርፋሪ እየለመነ እያደረ ነው።" ያሉት ፕሬዝዳንቱ የኑሮ ጫናው በተለይ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ተቀጥረው በሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። አክለውም ከዚህ በፊት በሰራተኞች የኑሮ ሁኔታ ዙርያ ከጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አህመድ ጋር ተደጋጋሚ  ውይይቶች መደረጋቸውን አስታውሰው ነገር ግን እነዚህ ውይይቶች ውጤት…
Read More
አቃቢ ህግ ለሽብር ወንጀል ተከሳሾች 96 ምስክሮች እንዳሉት ገለጸ

አቃቢ ህግ ለሽብር ወንጀል ተከሳሾች 96 ምስክሮች እንዳሉት ገለጸ

በእነ ዶክተር ወንደሰን አሰፋ መዝገብ ስር ክስ የተመሰረተባቸው ተጠርጣሪዎች ዛሬ ልደታ በሚገኘው ፍርድ ቤት ችሎት ቀርበዋል፡፡ በዚህ መዝገብ ስር ክስ ከተመሰረተባቸው እና በማረሚያ ቤት ከሚገኙ 23 ተጠርጣሪዎች መካከል ዶክተር ወንደሰን አሰፋ፣ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፣ ዳዊት በጋሻው፣ መስከረም አበራ፣ ገነት አስማማው እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡ በዚህ መዝገብ ስር 51 ተጠርጣሪዎች የሽብር ወንጀል ለመከላከል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1176/12 ጥሰዋል በሚል የሽብር ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በአዋጁ አንቀጽ 3/2 ሀ ላይ የተደነገገውን በመተላለፍ የሽብር ወንጀል ፈጽመዋል የሚል ክስ እንደደረሳቸው የተጠርጣሪዎች ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአል ዐይን ተናግረዋል፡፡ አቃቢ ህግ ባሳለፍነው ሰኞ ያሻሻለውን ክስ ለተጠርጣሪዎች እንዲደርሳቸው ያደረገ ሲሆን የተከሳሾችን እምነት ክህደት ቃል ለመቀበል በወቅቱ ባለመሟላታቸው ለዛሬ ህዳር…
Read More