Islam

2ኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና አዛን ውድድር ተጠናቀቀ

2ኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና አዛን ውድድር ተጠናቀቀ

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የበላይ ጠባቂነት በዘይድ ኢብኑ ሳቢት የቁርአን ማህበር አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 2ኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን የማጠቃሊያ ውድድር በአዲስ አበባ ስታዲየም ተካሂዷል። በማጠቃሊያ ውድድሩ በቁርዓን ሂፍዝ፣ በቁርዓን ቲላዋ እና በአዛን ዘርፍ አሸናፊ የሆኑ ተወዳዳሪዎች በዳኞች አማካኝነት ይፋ ሆነዋል። በዚህም በወንዶች የቁርአን ሂፍዝ ውድድር 1ኛ. ሙሐመድ ፉዓድ ከሊቢያ 2ኛ. ዩሱፍ አሺር … ከኳታር 3ኛ. አህመድ በሺር …ከአሜሪካ በሴቶች የቁርአን ሂፍዝ ውድድር 1ኛ ሩቅያ ሳላህ … ከየመን 2ኛ ነሲም ጀናዉጃ … አልጄሪያ 3ኛ ቀመራ ወሊዩ መሐመድ … ከኢትዮጵያ እንዲኁም በአዛን ውድድር 1ኛ ሙሀመድሻን አቡበከር … ከኢንዶኖዢያ 2ኛ ኡመር ዱራን … ከቱርክ 3ኛ አደም ጅብሪል ……
Read More
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የቁርዓን ውድድር ልታስተናግድ ነው

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የቁርዓን ውድድር ልታስተናግድ ነው

በኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ የቁርአን እና አዛን ውድድር ጥር 25 እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የቁርኣንና የአዛን ውድድር ሽልማት 2ኛ ዙር 2025 ውድድርን ምክንያት በማድረግ በርካታ ሀገራት እንግዶችና ቱሪስቶች በውድድሩ ላይ ለመታደም እንደሚመጡ የዘይድ እብን ሳቢት የቁርዓን ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ዶክተር ኑረዲን ቃሲም ተናግረዋል። የፊታችን ሰኞ ጥር 19 ቀን 2017 ከ 60 ሀገራት 100 ተወዳዳሪዎች እንዲሁም 11 ዳኞች ከሁሉም አህጉር ኢትዮጵያ የሚገቡ ሲሆን በአለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆኑ ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጣሪ የክብር እንግዶች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ ዳግም እንደሚገኙ ተገለጿል፡፡ ይህ መድረክ ቱሪስቶችን ወደ ኢትዮጵያ ለመሣብ ቀላል የማይባል ሚና ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የቱሪዝም ሚኒስትር፣ የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን…
Read More
ኢትዮጵያ የእስላማዊ አገራት ትብብር ድርጅትን ልትቀላቀል ነው ተባለ

ኢትዮጵያ የእስላማዊ አገራት ትብብር ድርጅትን ልትቀላቀል ነው ተባለ

ኢትዮጵያ ዋና መቀመጫውን ጅዳ ሳውዲ አረቢያ ካደረገው ዓለም አቀፉ የእስላማዊ ሀገራት ትብብር ድርጅት አባል ለመሆን እንቅስቃሴ መጀመሯ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ ከድርጅቱ አባል ሀገራት መካከል የተወሰኑትን ድጋፍ አግኝታለችም ተብሏል፡፡ የኦርጋናይዜሽን ኦፍ እስላሚክ ኮፕሬሽን  ወይም የእስላማዊ አገራት ትብብር ድርጅት 57 ሀገራትን በአባልነት የያዘ ስብስብ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የዚህ ድርጅት አባል ለመኾን ከድርጅቱ ጋር ንግግር መጀመሯን ዋዜማ ዘግቧል። በቻዳዊው ሂሴን ብራሂም ታሃ የሚመራው ድርጅቱ በዓለም ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቀጥሎ በአባላት ብዛት ትልቁ የበይነ መንግሥታት ማኅበር ነው። ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመኾን ንግግር የጀመረችው፣ ከድርጅቱ በቀረበላት ግብዣ መሠረት እንደኾነም ተገልጿል። ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመኾን በጀመረችው እንቅስቃሴ የቱርክን፣ ፓኪስታንን እና የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶችን ድጋፍ አግኝታለች ተብሏል። ከአፍሪካ ጅቡቲ፣…
Read More
ቱርክ በጦር መሳሪያ የተጎዳው አል ነጃሺ መስጅድን ለማደስ ጥያቄ አቀረበች 

ቱርክ በጦር መሳሪያ የተጎዳው አል ነጃሺ መስጅድን ለማደስ ጥያቄ አቀረበች 

 ታሪካዊው የኢትዮጵያ ቅርስ አል ነጃሺ መስጅድ በትግራይ ክልል የሚገኝ ሲሆን በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ወቅት በከባድ መሳሪያ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ ቱርክ ይህንን ታሪካዊ የእስልመና ቅርስ ለማደስ ለኢትዮጶያ መንግስት ጥያቄ እንዳቀረበች የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን  አስታውቋል፡፡ ሚኒስቴሩ እና የትግራይ ክልል ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ቅርሱ በሚታደስበት ሁኔታ ከቱርክ የቀረበውን ጥያቄ መቀበላቸው ተገልጿል፡፡ ቅርሱ በሚታደስበት ሁኔታም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጀምረዋል የተባለ ሲሆን የቱርክ ቅርስ ጥገና ባለሙያዎች ወደ ቦታው አምርተው ምልከታ መጀመራቸውን የቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አበባው አያሌው ተናግረዋል፡፡  ለቅርሱ እድሳት የሚያስፈልገው በጀት ምን ያህል እንደሆነ እና ምን ያህል ገንዘብ እንደሚፈጅ ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡ ለሁለት ዓመት በተካሄደው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት አል ነጃሺ መስጂድ…
Read More
በአዲስ አበባ አንዋር መስጅድ የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ

በአዲስ አበባ አንዋር መስጅድ የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ

በአዲስ አበባ መርካቶ አካባቢ ባለው አንዋር መስጅድ ዛሬ ምሳ ሰዓት አካባቢ የጸጥታ ችግር መከሰቱ ይታወቃል። ለአርብ ወይም ጁመዓ ጸሎት በስፍራው የነበሩ የእስልምና እምነት ተከታዮች እንዳሉን ከሆነ የሶላት ስነ ስርዓቱ ተጠናቆ ወደ ውጪ እየወጡ እያለ ከጸጥታ ሀይሎች ጥይት መተኮሱን ተከይሎ በአካባቢው ችግር ተፈጥሯል። ለደህንነቱ በመፍራት ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የአይን እማኝ ለአልዐይን እንዳለው " በአንዋር መስጅድ የጁመዓ ስግደትን ስግደት ጨርሰን ወደ ውጪ እየወጣን እያለ ፖሊሶች ጥይት ተኮሱ፣ ከዚያም ሰዎች መውደቅ እና መጮህ ጀመሩ" ሲል ነግሮናል። "አጠገቤ የነበሩ ሁለት ሰዎች እጅ እና እግራቸውን በጥይት ተመተው ሲወድቁ አይቻለሁ" ያለን ይህ የአይን እማኝ እኔ ወደ መስጅዱ ተመልሼ በመግባቴ ተርፌያለሁ ሲልም የአይን እማኙ አክሏል። "ምንም አይነት…
Read More
በአዲስ አበባ ለሰላማዊ ሰልፍ ወደ አደባባይ የወጡ ሁለት ሰዎች ህይወታቸው አለፈ

በአዲስ አበባ ለሰላማዊ ሰልፍ ወደ አደባባይ የወጡ ሁለት ሰዎች ህይወታቸው አለፈ

ፖሊስ በስፍራው በተፈጠረ ረብሻና ግርግር የሰው ሕይወት ማለፉን ገልጿል። በአዲስ አበባ ከተማ አንዋር መስጂድ የጁምዓ ሶላት ከተጠናቀቀ በኋላ በሌሎች አካባቢዎች መስጂዶች ፈርሰዋል በሚል ምክንያት በመርካቶ ዙሪያ በተፈጠረ ረብሻና ግርግር የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። ፖሊስ ባወጣው መግለጫ በተፈጠረው ረብሻና ግርግር ህግ በማስከበር መደበኛ ሥራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት መድረሱንም አስታውቋል። በተለይም በተለምዶ ጋዝ ተራ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ተፈጥሮ በነበረ ግርግር ሁለት ግለሰቦች ጉዳት ደርሶባቸው ለህክምና ሆስፒታል ከተላኩ በኋላ ሕይወታቸው አልፏል ተብሏል። በተጨማሪም አራት ግለሰቦች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ህግን ለማስከበር በተሰማሩ 37 የፖሊስ አመራርና አባላት እንዲሁም 15 የሚሆኑ የተለያዩ የፖሊስ አጋዥ ሀይሎች ከባድና ቀላል…
Read More