annualbudget

የፌደራል መንግስት 582 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ዓመታዊ በጀት አስጸደቀ

የፌደራል መንግስት 582 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ዓመታዊ በጀት አስጸደቀ

የዘንድሮ ዓመታዊ በጀት ወደ 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር አድጓል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መንግሥት ያቀረበው ተጨማሪ በጀት የተጋነነ ነው ሲሉ ወቅሰዋል፡፡ የፌደራል መንግስት ከስድስት ወር በፊት ለተያዘው በጀት ዓመት 970 ቢሊዮን ብር ዓመታዊ በጀት አጸድቆ ነበር፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የፌዴራል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት ተጨማሪ በጀት እንዲጸድቅለት በቀረበለት ጥያቄ ዙሪያ መክረዋል፡፡ ተጨማሪ በጀቱ ለዕዳ ክፍያ፣  ለማህበራዊ ድጋፍ፣ ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስተካከያ እንዲሆን መታሰቡን  በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መንግስት ተጠሪ ሚኒስትሩ ተስፋዬ ቤልጂጌ ተናግረዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት መንግስት ያቀረበው ተጨማሪ በጀት የተጋነነ ነው ሲሉ ተቃውሞ ቅርበዋል፡፡ ይሁንና ከ2017 አስከ 2021 ድረስ የተነደፈውን የማክሮ ኢኮኖሚ እና የፊስካል ፖሊሲ ማዕቀፍ…
Read More
የፌደራል መንግስት ዓመታዊ በጀት 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር ደረሰ

የፌደራል መንግስት ዓመታዊ በጀት 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር ደረሰ

መንግስት 550 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት አዘጋጅቷል ከሁለት ወር በፊት 970 ቢሊዮን ብር ዓመታዊ በጀት አጽድቆ የነበረው የፌደራል መንግስት ግማሽ ትሪሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) እንዳሉት የፌደራል መንግሥት 551 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርብ  ተናግረዋል። መንገስት ካቀረበው 550 ቢሊዮን ብር ውስጥ 240 ቢሊዮን ብሩ "ለማኅበራዊ ድጋፍ " የሚውል ነው የተባለ ሲሆን ቀሪው ደግሞ ለማህበራዊ ድጋፍ፣ ለምግብ ዋስትና፣ ለሰራተኛ ደመወዝ ጭማሪ፣ ለመድሃኒት ድጎማ፣ ለለነዳጅ ድጎማ እና ሌሎች መሰረታዊ ሸቀጦች ድጎማ እንደሚውል ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ የፌደራል መንግስት የበጀት ማስተካከያ ያደረገው ከዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ የገንዘብ ድጋፍ በብድር እና እርዳታ ማግኘቱን ተከትሎ ነው፡፡…
Read More
ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ዓመት 1 ትሪሊየን ብር አመታዊ በጀት መደበች

ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ዓመት 1 ትሪሊየን ብር አመታዊ በጀት መደበች

የሚንስትሮች ምክር ቤት በ34ኛ መደበኛ ስብሰባው የ2017 በጀት አመት የፌዴራል መንግስት ረቂቅ በጀት አዘጋጅቷል። የ2017 ዓ.ም የፌደራል መንግስት በጀት የአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነውን የ2016-2018 የልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችን እና የ2017-2021 የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚና የፊስካል ማዕቀፍን ማስፈጸም እንዲቻል በሚያደርግ መልኩ መዘጋጀቱን አስታውቋል። እንዲሁም የ2016 የፌደራል መንግስትን የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም መነሻ በማድረግ፤ የመንግስት የፋይናንስ አቅም እና ተጠባቂ ገቢዎችን ታሳቢ በማድረግ እንዲሁም አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የተሰጣቸውን ተልኮና ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስፈልጋቸውን ወጪ በመገምገም እንዲዘጋጅ መደረጉንም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በዚሁ መሰረት ለፌዴራል መንግስት መደበኛ ወጪዎች ፣ ለካፒታል ወጪዎች ፣ ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ…
Read More
ኢትዮጵያ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት 50 ቢሊዮን ብር በጀተች

ኢትዮጵያ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት 50 ቢሊዮን ብር በጀተች

በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት የሀገር መከላከያ በጀት ወጪ ከ120 ቢሊዮን ብር በላይ የደረሰ ሲሆን ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛው ሆኖ በታሪክ ተመዝግቧል። ለ2016 በጀት ዓመት ከቀረበው 801 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ የፌዴራል መንግሥት በጀት ውስጥ ለመከላከያ ሚኒስቴር 50 ቢሊዮን ብር ሲመደብ ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የወደሙ ተቋማትና አገልግሎቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ ደግሞ 20 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙ ተገልጿል። በ2015 በጀት ዓመት ውስጥ አጠቃላይ ከተበጀተው የመከላከያ ሚኒስቴር በጀት ድርሻ ከ12 ቢሊዮን በላይ ብር ደርሷል ተብሏል። የሰሜኑ ጦርነት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መፍትሔ ማግኘቱን ተከትሎ መከላከያ ሚኒስቴር ለ2016 በጀት ዓመት 50 ቢሊዮን ብር እንደተያዘለት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረበው የቀጣዩ ዓመት ረቂቅ በጀት ለመረዳት ተችሏል።…
Read More
የመንግሥት ዓመታዊ በጀት ጉድለት የ281 ቢሊዮን ብር ጭማሪ አሳየ

የመንግሥት ዓመታዊ በጀት ጉድለት የ281 ቢሊዮን ብር ጭማሪ አሳየ

ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የ2016 በጀት ዓመት አጠቃላይ የመንግሥት በጀት የ281 ቢሊዮን ብር ጉድለት እንደገጠመው የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሺዴ አስታውቀዋል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2016 በጀት ዓመት የመንግሥት በጀት 801.65 ቢሊዮን ብር እንዲሆን፤ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መምራቱ የሚታወስ ነው፡፡ ይህንኑ ተከትሎ ምክር ቤቱ የቀረበውን የበጀት ረቂቅ እየገመገመ ነው፡፡ የገንዘብ ሚኒስትሩ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት፤ መንግሥት ለ2016 ካረቀቀው አጠቃላይ በጀት ውስጥ የ281 ቢሊዮን ብር ጉድለት ማጋጠሙን ጠቁመዋል፡፡ የዓመቱ የበጀት ጉድለት በመጠናቀቅ ላይ ከሚገኘው የ2015 በጀት ዓመት የበጀት ጉድለት 50 ቢሊዮን ብር ገደማ ሆኗል፡፡ የ2015 በጀት ዓመት አጠቃላይ በጀት 786 ቢሊዮን ብር የነበረ ሲሆን፤ የበጀት ጉድለቱ 231 ቢሊዮን ብር መሆኑን ሚኒስትሩ…
Read More