ዜና

ኢትዮጵያ የሲንጋፖር ኩባንያን ወደ ሀገሯ እንዲመጣ ጋበዘች

ኢትዮጵያ የሲንጋፖር ኩባንያን ወደ ሀገሯ እንዲመጣ ጋበዘች

የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን በኢትዮጵያ በሎጀስቲክስ ኢንቨስትመንት እንዲሰማራ ጥሪ ቀረበ ዓለም አቀፍ የእስያ ኩባንያዎችን ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ እና ኢንቨስት እንዲያደርጉ ለማሳመን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ሲንጋፖርን በመጎብኘት ላይ ናቸው፡፡ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ ጋር በመሆን ሲንጋፖር የሚገኘውን የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን ጎብኝተዋል። ሁለቱ የኢንቨስትመንት አመራሮች ከሲንጋፖር ወደብ ባለስልጣን ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል። በውይይቱም የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን በኢትዮጵያ በሎጀስቲክስ ኢንቨስትመንት እንዲሰማራ ጠይቀዋል። የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ከፍተኛ ፍላጎት ገልፀው ባለስልጣኑ በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት የሚሰማራበትንና ልምድ የሚያካፍልበት መንገድ እንዲኖር ጥሪ አቅርበዋል። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ በበኩላቸው ፈጣን…
Read More
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆነው ተሾሙ

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆነው ተሾሙ

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆነው ተሾሙ ጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትምህርት ሚኒስትሩን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር አድርገው ሾሙ። ጠቅላይ ሚኒስተሩ ሹመቱን የሰጡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ እንዲቋቋም በ1294/23 የራስ ገዝ አዋጅ በረቀቀው መሠረት እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው 23ኛው መደበኛ ስብሰባ የዩኒቨርሲቲዎችን የራስ ገዝ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ተወያይቶ ማጽደቁን ተከትሎ ነው። በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ነጻነት እንዲረጋገጥ፣ ከፖለቲካዊም ሆነ አስተዳደራዊ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው የመማር ማስተማር እና የምርምር ሥራዎችን በላቀ መልኩ እንዲፈጽሙ እንዲሁም የሰው ሀብት እና የፋይናንስ አስተዳደር ነፃነትን በማረጋገጥ በሀገሪቱ የማኅበራዊ እና…
Read More
በደብረማርቆስ ከተማ በአራት ቀናት ውስጥ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በደብረማርቆስ ከተማ በአራት ቀናት ውስጥ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና ከተማ ደብረማረቆስ ከአርብ ነሐሴ 19/2015 እስከ ሰኞ ነሐሴ 22/2015 ድረስ በመከላከያ ሠራዊትና እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በተደረገ ውጊያ፤ ከመቶ በላይ ሰዎች ሳይገደሉ እንዳልቀረ ተገልጿል። ሥማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ የደብረማርቆስ ስፔሻላይዝድ ሆሰፒታል ሐኪም በከተማዋ ቦሌ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ከመቶ በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል ። የሟቾቹ አስክሬን ከኹለት ቀን በላይ ሳይነሳ መንገድ ላይ ወድቆ መታየቱንም ነዋሪዎች እና ሀኪሞች ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። "በቦታው የወደቁትን አስከሬኖች፤ አንዳንድ ሰዎች ሙስሊሙንም ክርስቲያኑንም ኹሉንም እያነሱ ማሪያም ቤተክርስቲያን ውስጥ እና በአካባቢ ቀብረዋቸዋል፡፡ ነገር ግን ሰኞ ድረስ ያልተቀበሩም ነበሩ።" ሲሉ ነዋሪዎቹ ጠቅሰዋል፡፡ በከተማው ለሦስት ቀናት በተደረገው ውጊያ ቆስለው ወደ ሆስፒታል የሄዱ ጥቂት ሰዎች ቢኖሩም፤ የትራንሰፖርት እና…
Read More
ዳሸን ባንክ ከሁለት የአውሮፓ ባንኮች 40 ሚሊዮን ዶላር ብድር አገኘ

ዳሸን ባንክ ከሁለት የአውሮፓ ባንኮች 40 ሚሊዮን ዶላር ብድር አገኘ

ዳሸን ባንክ ከእንግሊዝ እና ኔዘርላንድ ባንኮች 40 ሚሊዮን ዶላር ብድር አገኘ የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት (ቢ አይ አይ) እና የኔዘርላንድ የሥራ ፈጠራና ልማት ባንክ የሆነው (ኤፍ ኤም ኦ) እያንዳንዳቸው 20 ሚሊየን ዶላር በድምሩ 40 ሚሊየን ዶላር ብድር ለዳሸን ባንክ ማቅረባቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ የብድር አቅርቦቱ ኢትዮጵያ ለውጪ ገበያ የምታቀርበውን የግብርና ምርት ለማሳደግ እና በእጅጉ አስፈላጊ የሆነውን የውጪ ምንዛሬ አቅርቦት ለማሻሻል እንደሚያስችል ተመላክቷል፡፡ ቢ አይ አይ እና ኤፍኤምኦ ለዳሸን ባንክ ያቀረቡት ገንዘብ በኢትዮጵያ 80 በመቶ የህብረተሰብ ክፍል በተሰማራበት፣ ለጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት 39 በመቶ ድርሻ ላለው እና ለወጪ ንግዱ 90 በመቶ አስተዋጽኦ ለሚያበረክተው የግብርና ዘርፍ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረውም ታምኖበታል፡፡ የቀረበው ብድር ባንኩ…
Read More
ኢትዮጵያ በቡዳፔስት ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድር ላይ ስድስተኛ ሆና አጠናቀቀች

ኢትዮጵያ በቡዳፔስት ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድር ላይ ስድስተኛ ሆና አጠናቀቀች

ወደ ቡዳፔስት አቅንቶ የነበረው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ወደ አዲስ አበባ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ከነሀሴ 13 ቀን እስከ 21 ቀን 2015 ዓ.ም በሀንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስት ሲካሄድ የቆየው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ተጠናቋል። በዚህ ውድድር ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ 195 የዓለማችን ሀገራት የተሳተፉ ሲሆን ሜዳሊያ ማግኘት የቻሉ ሀገራት ግን 46 ብቻ ናቸው ተብሏል። ከማጣሪያ ውድድሮች ጀምሮ እስከ ፍጻሜ ድረስ 2 ሺህ 100 አትሌቶች በተሳፉበት በዚህ ውድድር ላይ 50 አትሌቶች የወርቅ ሜዳሊያዎችን ለሀገራቸው ሲያስገኙ 48 የብር እንዲሁም 50 የነሀስ ሜዳሊያዎችን ተወዳዳሪዎቹ ለሀገራቸው አስገኝተዋል፡፡ ውድድሩን 400 ሺህ ተመልካቾች በአካል ስታዲየም ገብተው ታድመውታል የተባለ ሲሆን ሀንጋሪ ደማቅ እና አይረሴ ውድድር ማዘጋጀቷ ተገልጿል። በዓለም አቀፉ…
Read More
የዓለም ባንክ ለኢትዮ-ጅቡቲ መንገድ 730 ሚሊዮን ዶላር ሰጠ

የዓለም ባንክ ለኢትዮ-ጅቡቲ መንገድ 730 ሚሊዮን ዶላር ሰጠ

የገንዘብ ሚኒስቴርና የዓለም ባንክ ለአፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ኮሪደር ፕሮጀክት (በኢትዮ-ጅቡቲ ኮሪደር ፕሮጀክት) የ730 ሚሊዮን ዶላር የድጋፍ ስምምነት መፈራረማቸው ይፋ ተደርጓል። ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያን 90 በመቶ የባህር ንግድን የሚይዘው ስትራቴጂካዊው ከአዲስ አበባ-ጅቡቲ ኮሪደር ጋር በተሳሰረ መልኩ የኢትዮጵያን የሎጅስቲክስና የትስስር አቅም እንደሚያጎለብት ተጠቁሟል። በስምምነቱ መሰረት ለሜኦሶ-ድሬዳዋ መንገድ ግንባታ የፋይናንስ ድጋፍ የሚደረግ ሲሆን፤ ግንባታው የትራንስፖርት አቅምና ብቃት የሚጨምር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል። መንገዱ በሚገነባባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎች የጤና፣ ውሃና ትምህርት አገልግሎት ተደራሽነት ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶች ድጋፍ እንደሚደረግም ተመላክቷል። ፕሮጀክቱ የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሺዬቲቭ አካልና የቀጣናዊ ትብብር ማዕቀፍ እንደሆነ ያመለከተው ሚኒስቴሩ፤ ማዕቀፉ አካባቢውን በመሰረተ ልማት የማስተሳሰር ፋይዳም እንዳለው ተጠቅሷል። ስምምነቱን የተፈራረሙትም የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ…
Read More
ድምጻዊ አቡሽ ዘለቀ አዲስ አልበሙን በአዲስ አበባ እንዳይሸጥ ተከለከለ

ድምጻዊ አቡሽ ዘለቀ አዲስ አልበሙን በአዲስ አበባ እንዳይሸጥ ተከለከለ

በኦሮሚኛ እና አማርኛ የሙዚቃ ስራዎቹ የሚታወቀው ድምፃዊ አቡሽ ዘለቀ አዲስ አልበም ለቋል። "እንዳባቴ እወድሻለሁ" በሚል ለገበያ ያቀረበው ይህ የአቡሽ ዘለቀ አዲስ አልበም በገበያ ላይ በመሸጥ ላይ መሆኑን አስታውቋል። ድምጻዊው በፌስቡክ ገጹ ላይ እንዳለው ምክኒያቱ ባልተገለጸበት ሁኔታ አልበሜ በአዲስ አበባ እንዳይሸጥ መከልከሉን ገልጿል። "እንደ አባቴ እወድሻለሁ" የተሰኘዉ አልበም በማህበራዊ መገናኛ መንገዶች ላይ በይፋ የተለቀቀ ቢሆንም በአዲስ አበባ ሲዲዉን የሚያዞሩ ወጣቶች መሸጥ እንዳይችሉ በፖሊስ መከልከላቸውንም ጠቅሷል። በትናንትናው እለት ሲዲዉን ለመሸጥ የወጡ ወጣቶች ከተከለከሉ በኋላም ድምፃዊዉ ክልከላዉ ለምን እንደተላለፈ አላዉቅም ብሏል። ድምፃዊዉ "ሁሉም ሰዉ ለኔ እኩል ነዉ ፤ በእኩልነት በአብሮነት ፣ በአንድነት የማምን ሰዉ ነኝ ያንን ሀሳብ ነዉ በአልበሜ ላይ ለማንጸባረቅ የሞከርኩት" ብሏል።…
Read More
አዲስ አበባ ቀጣዩን የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር እንድታካሂድ ተመረጠች

አዲስ አበባ ቀጣዩን የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር እንድታካሂድ ተመረጠች

የህዳሴው ግድብ የቴክኒክ ባለሙያዎች የሶስትዮሽ ድርድር ባለፉት ሁለት ቀናት በግብጽ ካይሮ መካሄዱን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በድንበር ተሻጋሪው አባይ ወንዝ ላይ እየገነባችው ያለው ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር በተለያዩ ምክንያቶች መቋረጡ ይታወሳል። ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የሶስትዮሽ ድርድር  ሲያካሂዱ ቆይተዋል። በሱዳን እና በኢትዮጵያ የተከሰተው የፖለቲካ አለመረጋጋት ለሶስትዮሽ ድርድር አለመቀጠል እና የግብጽ ተለዋዋጭ አቋም ማሳየት ለድርድሩ አለመሳካት ዋነኞቹ ምክንያቶች ነበሩ። ከአንድ ወር በፊት በግብጽ ካይሮ በሱዳን ለተከሰተው ጦርነት እልባት ለመፈለግ በሚል በተካሄደው የጎረቤት ሀገራት መድረክ ላይ ለመሳተፍ ወደ ስፍራው ያቀኑት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) እግረ መንገዳቸውን ከፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ  አልሲሲ ጋር መክረዋል። ሁለቱ መሪዎች ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከልም…
Read More
የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር በግብጽ ተጀመረ

የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር በግብጽ ተጀመረ

ኢትዮጵያ በድንበር ተሻጋሪው አባይ ወንዝ ላይ እየገነባችው ያለው ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር በተለያዩ ምክንያቶች መቋረጡ ይታወሳል። በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ሲካሄድ የቆየው ይህ የሶስትዮሽ ድርድር በኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳን መካከል ሲካሄድ ቆይቷል። በሱዳን እና በኢትዮጵያ የተከሰተው የፖለቲካ አለመረጋጋት ለሶስትዮሽ ድርድር አለመቀጠል እና የግብጽ ተለዋዋጭ አቋም ማሳየት ለድርድሩ አለመሳካት ዋነኞቹ ምክንያቶች ነበሩ። ከአንድ ወር በፊት በግብጽ ካይሮ በሱዳን ለተከሰተውን ጦርነት እልባት ለመፈለግ በሚል በተካሄደው የጎረቤት ሀገራት መድረክ ላይ ለመሳተፍ ወደ ስፍራው ያቀኑት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) እግረ መንገዳቸውን ከፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ጋር መክረዋል። ሁለቱ መሪዎች ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከልም የህዳሴው ግድብ ጉዳይ ዋነኛው ሲሆን በሶስት ወራት ውስጥ ዳግም ድርድር…
Read More
ኢትዮጵያ በሴቶች ማራቶን የወርቅና የብር ሜዳሊያ አገኘች

ኢትዮጵያ በሴቶች ማራቶን የወርቅና የብር ሜዳሊያ አገኘች

በሀንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስት አስተናጋጅነት እየተካሄደ ያለው የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ሰባተኛ ቀኑ ላይ ይገኛል፡፡ ዛሬ በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያ በአትሌት አማኔ በሪሶ አትሌት ጎቲቶም ገብረ ስላሴ የወርቅ እና ብር ሜዳሊያዎችን አግኝታለች፡፡ ሞሮካዊቷ አትሌት ፋጥማ ጋርዳዲ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ተጨማሪ ሜዳሊያ ልታገኝባቸው የምትችልባቸው ቀሪ ውድድሮች ያሉ ሲሆን አሁን ላይ በሁለት ወርቅ፣ በአራት ብር እና በሁለት ነሀስ በደምሩ በስምንት ሜዳሊያዎች ከዓለም በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ አሜሪካ በስምንት የወርቅ፣ ስፔን በአራት ወርቅ እንዲሁም ጃማይካ በሶስት የወርቅ ሜዳሊያ ከአንደኛ እስከ ሶተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ እና ነገ በሚካሄዱ የወንዶች ማራቶን፣ በሴቶች እና ወንዶች አምስት ሺህ ሜትር ውድድሮች ላይ የምትሳተፍ…
Read More