Worldathletics2023

የማራቶን ባለ ሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻውን ዙር ተቀላቀለች

የማራቶን ባለ ሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻውን ዙር ተቀላቀለች

አትሌት ትግስት አሰፋ ለአለም አትሌቲክስ በዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱ ምርጥ 10 የዓለም አትሌቶች መካከል አንዷነበረች። የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በ2023 ዓመት በተካሄዱ የተለያዩ ውድድሮች ላይ ስኬታማ የሆኑ አትሌቶችን ዝርዝር ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በመጀመሪያው ዙር 11 ምርጥ የዓለማችን አትሌቶች ዝረዝር ውስጥም የ5 ሺህ ሜትር ባለ ሪከርዷ ጉዳፍ ጸጋዬ እና የማራቶን ባለሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱ አትሌቶች ነበሩ። ዎርልድ አትሌቲክስ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት በውድድሩ ለመጨረሻ ዙር ያለፉ አትሌቶችን ዝርዝር አውጥቷል። በዚህም የማራቶን ባለሪከርዷ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለመጨረሻ ዙር ውድድር ከቀረቡ አትሌቶች መካከል እንዷ ሆናለች። ከአትሌት ትግስት አሰፋ በተጨማሪ ኬንያዊቷ አትሌት ፋይዝ ኪፕዬጎን፣ ጃማይካዊቷ ሸሪካ ጃክሰን፣ የኔዘርላንዷ…
Read More
ኢትዮጵያ በቡዳፔስት ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድር ላይ ስድስተኛ ሆና አጠናቀቀች

ኢትዮጵያ በቡዳፔስት ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድር ላይ ስድስተኛ ሆና አጠናቀቀች

ወደ ቡዳፔስት አቅንቶ የነበረው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ወደ አዲስ አበባ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ከነሀሴ 13 ቀን እስከ 21 ቀን 2015 ዓ.ም በሀንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስት ሲካሄድ የቆየው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ተጠናቋል። በዚህ ውድድር ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ 195 የዓለማችን ሀገራት የተሳተፉ ሲሆን ሜዳሊያ ማግኘት የቻሉ ሀገራት ግን 46 ብቻ ናቸው ተብሏል። ከማጣሪያ ውድድሮች ጀምሮ እስከ ፍጻሜ ድረስ 2 ሺህ 100 አትሌቶች በተሳፉበት በዚህ ውድድር ላይ 50 አትሌቶች የወርቅ ሜዳሊያዎችን ለሀገራቸው ሲያስገኙ 48 የብር እንዲሁም 50 የነሀስ ሜዳሊያዎችን ተወዳዳሪዎቹ ለሀገራቸው አስገኝተዋል፡፡ ውድድሩን 400 ሺህ ተመልካቾች በአካል ስታዲየም ገብተው ታድመውታል የተባለ ሲሆን ሀንጋሪ ደማቅ እና አይረሴ ውድድር ማዘጋጀቷ ተገልጿል። በዓለም አቀፉ…
Read More
ኢትዮጵያ በሴቶች ማራቶን የወርቅና የብር ሜዳሊያ አገኘች

ኢትዮጵያ በሴቶች ማራቶን የወርቅና የብር ሜዳሊያ አገኘች

በሀንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስት አስተናጋጅነት እየተካሄደ ያለው የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ሰባተኛ ቀኑ ላይ ይገኛል፡፡ ዛሬ በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያ በአትሌት አማኔ በሪሶ አትሌት ጎቲቶም ገብረ ስላሴ የወርቅ እና ብር ሜዳሊያዎችን አግኝታለች፡፡ ሞሮካዊቷ አትሌት ፋጥማ ጋርዳዲ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ተጨማሪ ሜዳሊያ ልታገኝባቸው የምትችልባቸው ቀሪ ውድድሮች ያሉ ሲሆን አሁን ላይ በሁለት ወርቅ፣ በአራት ብር እና በሁለት ነሀስ በደምሩ በስምንት ሜዳሊያዎች ከዓለም በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ አሜሪካ በስምንት የወርቅ፣ ስፔን በአራት ወርቅ እንዲሁም ጃማይካ በሶስት የወርቅ ሜዳሊያ ከአንደኛ እስከ ሶተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ እና ነገ በሚካሄዱ የወንዶች ማራቶን፣ በሴቶች እና ወንዶች አምስት ሺህ ሜትር ውድድሮች ላይ የምትሳተፍ…
Read More