Hungary

ኢትዮጵያ በሴቶች ማራቶን የወርቅና የብር ሜዳሊያ አገኘች

ኢትዮጵያ በሴቶች ማራቶን የወርቅና የብር ሜዳሊያ አገኘች

በሀንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስት አስተናጋጅነት እየተካሄደ ያለው የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ሰባተኛ ቀኑ ላይ ይገኛል፡፡ ዛሬ በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያ በአትሌት አማኔ በሪሶ አትሌት ጎቲቶም ገብረ ስላሴ የወርቅ እና ብር ሜዳሊያዎችን አግኝታለች፡፡ ሞሮካዊቷ አትሌት ፋጥማ ጋርዳዲ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ተጨማሪ ሜዳሊያ ልታገኝባቸው የምትችልባቸው ቀሪ ውድድሮች ያሉ ሲሆን አሁን ላይ በሁለት ወርቅ፣ በአራት ብር እና በሁለት ነሀስ በደምሩ በስምንት ሜዳሊያዎች ከዓለም በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ አሜሪካ በስምንት የወርቅ፣ ስፔን በአራት ወርቅ እንዲሁም ጃማይካ በሶስት የወርቅ ሜዳሊያ ከአንደኛ እስከ ሶተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ እና ነገ በሚካሄዱ የወንዶች ማራቶን፣ በሴቶች እና ወንዶች አምስት ሺህ ሜትር ውድድሮች ላይ የምትሳተፍ…
Read More