Fano

አሜሪካ ፋኖ እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የሰላም እቅዳቸውን እንዲያሳውቁ ጠየቀች

አሜሪካ ፋኖ እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የሰላም እቅዳቸውን እንዲያሳውቁ ጠየቀች

አሜሪካ ዛሬ አዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ በኩል ለፌዴራል መንግሥት እና ለታጣቂዎች መልዕክት አስተላልፋለች። በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ዛሬ ባስተላለፉት መልዕክት በመላው ኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለጉዳት የዳረጉ ግጭቶች ሰላማዊና ትክክለኛ መፍትሔ እንዲፈለግላቸው መልዕክት አስተላልፈዋል። አምባሳደሩ፥ ለታጣቂ ኃይሎች እና ለፌደራል መንግስት ባስተላለፉት መልዕክት ህዝብን እንዲያስቀድሙ ጥሪ አቅርበዋል። " ጦርነቱን ማቆም፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ መርዳት እና ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ እና የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ ነው " ሲሉ አስገንዝበዋል። " በትጥቅ ትግል ስም የሚፈጸሙ ህገወጥ እና የኃይል እርምጃዎች ሊቆሙ ይገባል " ብለዋል። አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በመልዕክታቸው ለፋኖ ፣ ለኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) እና ለፌደራል መንግስት የተናጠል መልዕክት…
Read More
በአማራ ክልል ደብረሲና እና አዴት ከተሞች ከ27 በላይ ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ተገደሉ

በአማራ ክልል ደብረሲና እና አዴት ከተሞች ከ27 በላይ ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ተገደሉ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “የመንግሥት ኃይሎች” ቤት ለቤትና መንገድ ላይ ‘ሰላማዊ ሰዎችን’ መግደላቸውን የዐይን እማኞችና ነዋሪዎች ተናግረዋል። ጥቃቶቹ ሰኞ ሰኔ 17 እና ረቡዕ ሰኔ 19፤ 2016 ዓ/ም መፈጸማቸው የተነገረ ሲሆን፤ በጥቃቶቹም ከ27 በላይ ንጹሃን ሰዎች እንደተገደሉ ተገልጿል። በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ ሾላ ሜዳ በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሰኔ 19 በመንግሥት ኃይሎች ደርሷል በተባለ ጥቃት ቢያንስ 15 ሰዎች መገደላቸውን እና አራት የሚሆኑ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል። በከተማዋ ‘አጋም በር መገንጠያ’ በተባለ ሰፈር ጥቃቱ ምሽት 11፡30 አካባቢ እንደተፈጸመ የተናገሩ አንድ ከጥቃቱ የተረፉ እማኝ፤ በጥቃቱ በአብዛኛው ማዳበሪያ ለመውሰድ…
Read More
በአማራ ክልል ጅጋ ከተማ 18 ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ተገደሉ

በአማራ ክልል ጅጋ ከተማ 18 ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ተገደሉ

የጸጥታ ሀይሎቹ የአዕምሮ ህመምተኛን ጨምሮ በመዝናናት ላይ የነበሩ የባንክ ሰራተኞችን እና መምህራንን ገድለዋል በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ጅጋ ከተማ፤ ቢያንስ 18 ሰዎች “በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን” ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ብሔራዊው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤ “በአካባቢው ጥቃት ተፈጽሟል” የሚል መረጃ እንደደረሰው ገልጾ ፤ ክስተቱን እያጣራ መሆኑን አስታውቋል። የዓይን እማኞቹ፤ የጅጋ ከተማ ነዋሪዎች የተገደሉበት ክስተት የተፈጸመው ባሳለፍነው እሁድ ሰኔ 9፤ 2016 አመሻሽ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። በዚሁ ዕለት ምሽት 11 ሰዓት ገደማ፤ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን የጫኑ “ሶስት ፓትሮል” ተሽከርካሪዎች ከደንበጫ ወደ ጅጋ ከተማ እየገቡ በነበረበት ወቅት፤ “በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት” ከፊት በነበረው መኪና ላይ ጥቃት ካደረሱ በኋላ መሸሻቸውን የዓይን እማኞቹ አብራርተዋል። ጥቃት…
Read More
በባህርዳር 17 ንጹሃን ዜጎች በሀገር መከላከያ ሰራዊት ከህግ ውጪ መገደላቸው ተገለጸ

በባህርዳር 17 ንጹሃን ዜጎች በሀገር መከላከያ ሰራዊት ከህግ ውጪ መገደላቸው ተገለጸ

አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው ሪፖርት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባህር ዳር ንጹሃንን ከህግ አግባብ ውጪ ገድሏል ብሏል። ተቋሙ በአማራ ክልል ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት አስመልክቶ ሰፋ ያለ ሪፖርቱን አውጥቷል። በአቡነ ሃራ፣ ልደታ እና ሳባ ታሚት በተባሉ አካባቢዎች ከ17 በላይ ንጹሃን በመከላከያ ተተኩሶባቸው መገደላቸውን ከአይን እማኞች ማረጋገጡን የጠቆመው አምነስቲ ኢንተርናሽናል አንዳንድ ቤተሰቦቻቸው የተገደሉባቸው ሰዎች አስከሬን መውሰድ እና መቅበር ተከልክለዋል ተብሏል፡፡ ሪፖርቱ በአማራ ክልል የመከላከያ ሰራዊትና የፋኖ ታጣቂዎች ውጊያ እንደጀመሩና ከሶስት ወር በኋላ በባህር ዳር ተፈጸሙ የተባሉ ግድያዎችን ብቻ የቃኘ ነው። የኢንተርኔት አገልግሎት መዘጋት እና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ያስከተላቸው ክልከላዎች በአማራ ክልል እየተካሄደ ባለው ጦርነት የተፈጸመውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በዝርዝር…
Read More
በአማራ ክልል መራዊ ከተማ ከ50 በላይ ንጹሃን ዜጎች በመከላከያ ሰራዊት ተገደሉ

በአማራ ክልል መራዊ ከተማ ከ50 በላይ ንጹሃን ዜጎች በመከላከያ ሰራዊት ተገደሉ

ከአማራ ክልል ዋና ከተማ ከሆነችው ባህርዳር በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው መራዊ ከተማ ከሰሞኑ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከባድ ውጊያ ተቀስቅሶ ነበር፡፡ በዚህ ውጊያ ምክንያት የፋኖ ታጣቂዎች የመራዊ ከተማን ተቆጣጥረው የነበረ ቢሆንም በኋላ ለቀው መሄዳቸውን ተከትሎ ወደ ከተማው የገባው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ50 በላይ የከተማዋ ነዋሪዎችን እንደገደሉ ቢቢሲ ነዋሪዎችን አነጋግሮ ዘግቧል፡፡ እንደ ነዋሪዎቹ አስተያየት ከሆነ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ነዋሪዎቹን ከመንገድ ላይ እና መኖሪያ ቤታቸው በማሰባሰብ ገድለዋቸዋል፡፡ በአማራ ክልል በርካታ አካባቢዎች ከባድ ውጊያ እየተካሄደ ሲሆን የፋኖ ታጣቂዎች በተለይም የገጠር አካባቢዎችን ተቆጣጥረው ሲያዙ ከተሞች ደግሞ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ተይዘዋል፡፡ ባሳለፍነው ዓመት ሚያዚያ ወር የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ ለማደራጀት…
Read More
የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ጃል መሮ ፊት ለፊት ተገናኙ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ጃል መሮ ፊት ለፊት ተገናኙ

የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራር እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት መሪው ጃል መሮ ፊት ለፊት መገናኘታቸው ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂ ቡድን መካከል በታንዛኒያ የሁለተኛ ዙር የሰላም ንግግር መጀመራቸው ተሰምቷል። ቢቢሲ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ባወጣው ዘገባ የሰላም ንግግሩ ጥቂት ቀናትን እንዳስቆጠረና ከሁለቱም ወገኖች የተወጣጡ የጦር አባላት ተወካዮች በተገኙበት በመካሄድ ላይ ይገኛል። ከዚህ ቀደም ራስ ገዝ ግዛት በሆነችው ዛንዚባር የተካሄደውን ድርድር የምሥራቅ አፍሪካ በየነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ)፣ አሜሪካ፣ ኖርዌይ እና ኬንያ አስተባባሪ እና አሸማጋይ ሚና መውሰዳቸው ይታወሳል። አሁን የተጀመረውን ንግግር ማን እንደሚያደራድር ግልጽ ባይሆንም፣ ኢጋድ ከዚህ ቀደም የነበረውን ሚና ሳያስቀጥል እንዳልቀረ ተጠቅሷል። ከዚህ በተጨማሪ አዲስ…
Read More
በአማራ ክልል ንጹሀን ዜጎች ከፍርድ ውጪ እየተገደሉ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

በአማራ ክልል ንጹሀን ዜጎች ከፍርድ ውጪ እየተገደሉ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሚያዝያ ወር 2015 ጀምሮ በአማራ ክልል የሚታየውን የጸጥታ ችግር እንዳሉ አስታውቋል። ኮሚሽኑ እንዳለው በክልሉ የነበረው የጸጥታ ችግሩ ወደ ትጥቅ ግጭት ማምራቱን ተከትሎ የንጹሀን ዜጎች ግድያ እና እንግልት ቀጥሏል ብሏል። በተለይም ከነሐሴ 19 እስከ ነሐሴ 30/2015 ድረስ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በርካታ ንጹሃን መሞታቸውን እና ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን ኢሰመኮ በመግለጫው አስታውቋል። "በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስ ከተማ፣ በሰሜን ጎጃም ዞን አዴትና መራዊ፣ በደቡብ ጎንደር ዞን ደብረ ታቦር፣ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ደልጊ፣ በሰሜን ሸዋ ዞን ማጀቴ፣ ሸዋ ሮቢት እና አንጾኪያ ከተሞች እና በአካባቢዎቻቸው በሚገኙ አንዳንድ የገጠር ቀበሌዎች በግጭቱ በርካታ ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል ተብላል። እንዲሁም ለአካል ጉዳት እና የንብረት…
Read More
በአማራ ክልል በአንድ ቀን ብቻ ከ49 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል በአንድ ቀን ብቻ ከ49 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ከትናንት በስቲያ ሰኞ ነሐሴ 29 ቀን 2015 የመንግሥት የጸጥታ አካላት በወሰዱት እርምጃ እንዲሁም በድሮን ጥቃት ከ49 በላይ ንጹሃን መገደላቸውን እናት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፓርቲው በመግለጫው ሰኞ ነሐሴ 29 ቀን 2015 በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ማጀቴ ከተማ የመንግሥት ወታደሮች በወሰዱት እርምጃ 29 ንጹሃን ዜጎች በየመኖሪያ ቤታቸው በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ብሏል፡፡ "ከሟቾች ውስጥም ሕጻናት፣ ወጣቶች እና አረጋውያን እንዳሉበት ከመረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠናል።" ያለው ፓርቲው  "በተመሳሳይ ነሐሴ 29 ቀን 2015 በምስራቅ ጎጃም ዞን ቢቡኝ ወረዳ፣ ሞሰባ ሽሜ አቦ ቀበሌ አዳራሽ ጎጥ ላይ መንግሥት በፈጸመው የድሮን ጥቃት ከ11 በላይ ንጹሐን ዜጎች ተጨፍጭፈዋል።" ብሏል። በዚሁ ቀን በምዕራብ ጎጃም ዞን ደጋ ዳሞት ወረዳ…
Read More
በደብረማርቆስ ከተማ በአራት ቀናት ውስጥ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በደብረማርቆስ ከተማ በአራት ቀናት ውስጥ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና ከተማ ደብረማረቆስ ከአርብ ነሐሴ 19/2015 እስከ ሰኞ ነሐሴ 22/2015 ድረስ በመከላከያ ሠራዊትና እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በተደረገ ውጊያ፤ ከመቶ በላይ ሰዎች ሳይገደሉ እንዳልቀረ ተገልጿል። ሥማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ የደብረማርቆስ ስፔሻላይዝድ ሆሰፒታል ሐኪም በከተማዋ ቦሌ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ከመቶ በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል ። የሟቾቹ አስክሬን ከኹለት ቀን በላይ ሳይነሳ መንገድ ላይ ወድቆ መታየቱንም ነዋሪዎች እና ሀኪሞች ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። "በቦታው የወደቁትን አስከሬኖች፤ አንዳንድ ሰዎች ሙስሊሙንም ክርስቲያኑንም ኹሉንም እያነሱ ማሪያም ቤተክርስቲያን ውስጥ እና በአካባቢ ቀብረዋቸዋል፡፡ ነገር ግን ሰኞ ድረስ ያልተቀበሩም ነበሩ።" ሲሉ ነዋሪዎቹ ጠቅሰዋል፡፡ በከተማው ለሦስት ቀናት በተደረገው ውጊያ ቆስለው ወደ ሆስፒታል የሄዱ ጥቂት ሰዎች ቢኖሩም፤ የትራንሰፖርት እና…
Read More
የጠቅላይ ሚንስትሩ የቀድሞ አማካሪ በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ በሀይል እንደማይፈታ ተናገሩ

የጠቅላይ ሚንስትሩ የቀድሞ አማካሪ በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ በሀይል እንደማይፈታ ተናገሩ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሁለት ሳምንት በፊት በሚንስትሮች ምክር ቤት የተወሰነውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጽድቋል። ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት የቀድሞው የጠቅላይ ሚንስትሩ የደህንነት አማካሪ፣ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር እና የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለምክር ቤቱ አባላት ንግግር አድርገዋል። አቶ ገዱ ከሌሎች የምክር ቤቱ አባላት ለየት ባለ መልኩ በአማራ ክልል ስላለው ሁኔታ ባደረጉት ንግግር ከምክር ቤቱ አባላት ተቃውሞ ገጥሟቸው ተቋርጧል። አቶ ገዶ ንግግራቸው እስከተቋረጠበት ጊዜ ድረስ ባደረጉት ንግግር " ብልጽግና መራሹ መንግሥት ራሱ የፖለቲካ ችግር እየፈጠረ ነው" ብለዋል። "ፓርቲው የፈጠረውን የፖለቲካ ችግር ለመፍታት የሚሞክረው ከፖለቲካዊ መፍትሄ ይልቅ ወታደራዊ መፍትሄ ሆኗል" የሚሉት አቶ ገዱ ብልጽግና ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ…
Read More