ዜና

በኢትዮጵያ ከ4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መፈናቀላቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከ4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መፈናቀላቸው ተገለጸ

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ተቋም (IOM) ከባለፈው ሕዳር እስከ ሰኔ ወር ድረስ በ3 ሺሕ 300 መጠለያ ጣቢያዎች ሰበሰብኩት ባለው መረጃ፤ በኢትዮጵያ ከ11 ክልሎች ከ4 ነጥብ 38 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ከነዚህ ተፈናቃዮች 66 በመቶ የሚሆኑት በግጭት ምክንያት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ቀሪዎቹ በድርቅ እና በማህበራዊ ችግሮች ምክንያት መፈናቀላቸው ተገልጿል፡፡ሶማሌ ክልል በድርቅ ምክንያት የተፈናቀሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች መገኛ መሆኑ ሲገለጽ፤ ትግራይ፣ አማራ ፣ኦሮሚያ እና አፋር ክልሎች በግጭት የተፈናቀሉ ዜጎች ያሉባቸው አካባቢዎች ናቸው ተብሏል፡፡ በተመሳሳይ በ10 ክልሎች ተፈናቃዮችን ለመመለስ በተደረገ ጥናት 3 ነጥብ 24 ሚሊዮን ተፈናቃዮች ወደ ቦታቸው መመለስ ይችላሉ በሚል መለየታቸውም ተገልጿል፡፡ተቋሙ አክሎም በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተፈናቃዮች የተመለሱባቸው…
Read More
ከኬንያ ላሙ ወደብ ሞያሌ- አዲስ አበባ የባቡር መስመር ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

ከኬንያ ላሙ ወደብ ሞያሌ- አዲስ አበባ የባቡር መስመር ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን የባቡር መስመር በ14 ቢሊዮን ዶላር ልትዘረጋ መሆኑን አስታውቃለች፡፡ ኬንያ የምትዘረጋው ይህ ፈጣን የባቡር መስመር በኤሌክትሪክ የሚሰራ ሲሆን፤ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ ላሙ ወደብ በማድረግ ኢትዮጵያን እና ደቡብ ሱዳንን እንደሚያገናኝ ብሉምበርግ ዘግቧል። በዓይነቱ ልዩ ነው የተባለው ይህ የባቡር መስመር በፈረንጆቹ 2025 ሥራ እንደሚጀመር እና 3 ሺሕ ከሎ ሜትር እንደሚረዝም ታውቋል፡፡ የባቡር መስመሩ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ አድርጎ፣ በኬንያዋ ማዕከላዊ ከተማ ኦሲዮሎን በኩል፣ ናይሮቢን እና አዲስ አበባን በማገናኘት የመጨረሻም መዳረሻውን ደቡብ ሱዳን ጁባ እንደሚያደርግ ተነግሯል፡፡ ይህ ፈጣን የባቡር መስመር “ኢትዮጵያ በአሰብ እና ምጽዋ እንዲሁም ጅቡቲ ወደቦች ላይ ያላትን ጥገኝነት የሚቀንስ ነው” የተባለ ሲሆን፤ ሌሎች በርካታ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች…
Read More
አሸዋ ቴክኖሎጂ  ተጨማሪ የአክስዮን ሽያጭ ጀመረ

አሸዋ ቴክኖሎጂ ተጨማሪ የአክስዮን ሽያጭ ጀመረ

አክስዮን ገዢዎች  በ500 ሺ ብር  አክስዮን በስድስት አመት ውስጥ ከስድስት ሚልየን ብር በላይ እንደሚያገኙ ተገልጿል። አሸዋ ቴክኖሎጂ በሰው ሃብት አስተዳደር ፣ በሂሳብ መዝገብ አያያዝ  እና የቢዝነስ  ክንውኖችን ማቀላጠፊያ ሶፍትዌሮችን በማበልጸግ ወደ ስራ የገባ አገር በቀል ድርጅት ነው። የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዳንኤል በቀለ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ግለሰቦች እና ድርጅቶች አክስዮን  ገዝተው ትርፍ የሚጋሩበትን ለሶስት ወራት የሚቆይ የአክስዮን ሽያጭ መጀመሩን ተናግረዋል። የአንድ አክስዮን ዋጋ 2 ሺህ 500 ብር እየሸጠ ያለው አሸዋ ቴክኖሎጂ  ትንሹ አክስዮን 500 ሺህ ብር ሲሆን  ትልቁ አክስዮን ደግሞ 100 ሚልየን ብር እንደሆነ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተጠቅሷል። የአክስዮን ገዢዎች የገዙትን አክስዮን መጠን 50 በመቶውን ቅድሚያ መክፈል ይጠበቅባቸዋል የተባለ ሲሆን ቀሪ የአክስዮን ድርሻዎችን ደግሞ…
Read More
የብሪክስ መሪዎች ዓመታዊ ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ መካሄድ ጀመረ

የብሪክስ መሪዎች ዓመታዊ ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ መካሄድ ጀመረ

ከ15 ዓመት በፊት በብራዚል፣ ሩሲያ፣ሕንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የተመሰረተው ብሪክስ የዘንድሮውን ጉባኤ በጆሀንስበርግ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ የመሪዎች ጉባኤ ላይ የቻይና ፕሬዝዳንት ሺ ፒንግ፣ የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ፣ የብራዚል ፕሬዝዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ እና የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ ተገኝተዋል፡፡ ሩሲያ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሰርጊ ላቭሮቭ የተወከለች ሲሆን ፕሬዝዳንት ፑቲን በበይነ መረብ ታግዘው ንግግር አድርገዋል፡፡ የጉባአው አዘጋጅ ደቡብ አፍሪካ ለ60 ሀገራት ግብዣ ያቀረቡ ሲሆን ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በጉባኤው ላይ እንዲገኙ መጋበዛቸውን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ40 በላይ የዓለማችን ሀገራት የብሪክስ አባል ለመሆን ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ሳውዲ አረቢያ፣ ኢራን፣ የተባበሩት አረብ አምሬት፣ ግብጽ፣ አልጀሪያ እና ሌሎችም ሀገራት ብሪክስን ለመቀላቀል በይፋ…
Read More
በአማራ ክልል ከ50 በላይ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ከ50 በላይ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለዉ ጦርነት ምክንያት ክልሉ ከመንግሥት መዋቅር ውጪ ናቸው የተባሉ ወረዳዎች ይፋ ሆነዋል። መንግስት ከቁጥጥር ውጪ የሆኑ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳድር የባንክ ሂሳቦችን እንዳይንቀሳቀሱ እገዳ ጥሏል። ከሰሜን ሸዋ ወረዳዎች ውስጥ ሚዳ ወረሞ፣ መርሃቤቴ፣ አለም ከተማ ፣እነዋሪ፣ መንዝ ቀያ፣ መንዝ ላሎ፣ መንዝ፣ ማማ፣ መንዝ ሞላሌ ከተማ አስተዳድር፣ መንዝ ጌራ፣ ሲያደብር እና ዋዩ፣ እንሳሮ ፣ሞረትና ጅሩ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ናቸው ተብሏል። ከሰሜን ወሎ ወረዳዎች ደግሞ ግዳን ወረዳ ፣እስታይሽ፣ ቡግና እና ሙጃ ወረዳዎች እንዲሁም ከደቡብ ወሎ ደፍሞ ወግዲ ወረዳ፣ ከለላ፣ መካነሰላም ፣ቦረና ፣ አማራ ሳይንት እና ዋድላ ደላንታ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ናቸው የተባለ ሲሆን የመንግስት ተቋማት የባንክ ሂሳብ እንዳይንቀሳቀሱ እገዳ…
Read More
አፍሪካ ህብረት ኒጀርን ከአባልነት አገደ

አፍሪካ ህብረት ኒጀርን ከአባልነት አገደ

የአፍሪካ ህብረት ከአንድ ወር በፊት መፈንቅለ መንግስት ያደረገችው ኒጀርን ከአባልነት አግዷል። በጀነራል ቲያኒ የሚመራው የኒጀር ጦር በምርጫ ስልጣን በያዙት የኒጀር ፕሬዝዳንት ባዙም ላይ በመፈንቅለ መንግሥት ስልጣን ተቆጣጥሯል። ይህን ተከትሎ የአፍሪካ ህብረት ኒጀርን ከአባልነት ላልተወሰነ ጊዜ ከስልጣን ማንሳቱን አስታውቋል። የመፈንቅለ መንግስቱ መሪዎች በምርጫ ስልጣን የያዙትን ፕሬዚዳንት መሃመድ ባዙምን ከእስር እንዲፈቱ እና ወደ ቤታቸው እንዲመልሱም ህብረቱ ጥሪ አቅርቧል። የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና የፀጥታው ምክር ቤት የምዕራብ አፍሪካ ህብረት (ኢኮዋስ) ለወታደራዊ ጣልቃ ገብነት ተጠባባቂ ሃይል ለማንቀሳቀስ ያሳለፈውን ውሳኔ መመልከቱንም ሬውተርስ ዘግቧል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እንደዚህ አይነት ሃይል ማሰማራት ያለውን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና የደህንነት አንድምታ እንዲገመግም ጠይቋል። የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማህበረሰብ (ኢኮዋስ) ዲሞክራሲን…
Read More
ኢትዮጵያ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ

በ2015 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የሚኒስቴሩ የኮሙኒኬሽንና የሕዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ አለማየሁ ጌታቸው እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተለይም አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን ከማልማት እንዲሁም ነባሮችን ከማደስ እና ከመጠገን አንጻር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተዋል፡፡ የጮቄ ተራራ እና ወንጪ የኢኮ ቱሪዝም መዳረሻዎች በዓለም ቱሪዝም ድርጅት እውቅና እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉንም አስታውሰዋል። በተለያዩ አካባቢዎች ተጨማሪ የኢኮ ቱሪዝም መዳረሻ ሊሆኑ የሚችሉ ቦታዎችን በጥናት የመለየት እና መረጃ የማሰባሰብ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡ በበጀት ዓመቱም በርካታ ቁጥር ካላቸው የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 61 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ነው አቶ አለማየሁ…
Read More
ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፕላን ጥገና ፈቃድ ሰጠች

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፕላን ጥገና ፈቃድ ሰጠች

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፕላን ጥገና ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ ባለስልጣኑ ዋን ኤም. አር.ኦ (One M.R.O) ለተሰኘ የግል ተቋም በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሆነውን አውሮፕላን ጥገና ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ በ2013 ዓ.ም የቢዝነስ ፈቃድ አውጥቶ የተቋቋመው ዋን ኤም. አር.ኦ የጥገና ፈቃድ ሰርትፊኬት ለማግኘት የበቃው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ያዘጋጃቸውን አምስት ዓለም አቀፍ መስፈርቶች አሟልቷል በሚል ነው፡፡ ለተቋሙ የተሰጠው የጥገና ፈቃድ ቦይነግ 737 ክላሲክና ቦይንግ 737 ኔክስት ጄኔሬሽን የተባሉ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን መጠገን ያስችለዋል ተብሏል፡፡ ዋን ኤም.አር ኦ. የጥራት ማረጋገጫና ደህንነት ማናጀር አቶ አንዱአለም ስለሺ ፤ ድርጅታቸው በአሁን ሰዓት ናይጄሪያ ላይ መሰረት አድርጎ በምዕራብ አፍሪካ ለሚገኙ የግል ኦፐሬተሮች የጥገና አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ድርጅታቸው በቀጣይም በኢትዮጵያ…
Read More
የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፈ

የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፈ

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ በተያዘው ዓመት ውስጥ 42 ቢሊየን ብር ገቢ አግኝቻለሁ ያለ ሲሆን ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቋል። ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት ደግሞ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን አመልክቷል። የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንዳሉት ኮቪድ 19፣ የዩክሬንና ሩሲያ ጦርነት፣ የሀገር ውስጥ ፀጥታ ችግርና ሌሎች ችግሮች በድርጅቱ ስራዎች ላይ ተፅዕኖ ነበራቸው። በበጀት ዓመቱ ከውጭ ወደ አገር ውስጥ ከተጓጓዘው 7 ነጥብ 4 ሚሊየን ቶን እቃ ውስጥ 34 በመቶውን የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ማጓጓዙን ገልጸዋል። በመርከብ የወጪ ጭነትና ጥቅል ጭነት አገልግሎት በእቅዱ ልክ መፈፀሙን ጠቅሰው፣ በብረት ማጓጓዝ ረገድ ግን ዝቅተኛ…
Read More
እስራኤል የኢትዮጵያን ሁኔታ የሚከታተል የጦር መሪ ሾመች

እስራኤል የኢትዮጵያን ሁኔታ የሚከታተል የጦር መሪ ሾመች

ብርጋዴር ጀነራል ሀርል ክንፎ በኢትዮጵያ ያሉ ቤተ እስራኤላዊያንን ጉዳይ እንዲከታተሉ መሾማቸው ተገልጿል። እንደ ጀሩሳሌም ፖስት ዘገባ ከሆነ የእስራኤል መንግሥት በኢትዮጵያ የሚገኙ ቤተ እስራኤላዊያን የሚያነሱትን ቅሬታ የሚከታተልና የመፍትሔ ሀሳብ የሚያቀርብ ወታደራዊ መሪ መሾሙ ተገልጿል። ጀነራሉ የእስራኤል አሊያስ እና የውህደት ሚኒስቴር በኩል እንደተሾሙ የተገለጹ ሲሆን ኢትዮጵያን በተመለከተ የእስራኤልን ወቅታዊ የስደት ፖሊሲ የሚገመግም ቡድን እንዲያዋቅሩም ተጨማሪ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል ተብሏል። ከአገሪቱ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ይሁንታ በመጠባበቅ ላይ ያሉት ጀነራሉ የጥናት ቡድኑ በአዲስ አበባ እና በጎንደር ወደ እስራኤል ለማቅናት በሚጠባበቁ ቤተ እስራኤላውያንን መርዳት ዋነኛ ስራቸው እንደሚሆንም በዘገባው ላይ ተጠቅሷል። ብርጋዴር ጄኔራል ሃርል ከዚህ ቀደም በእስራኤል ቁልፍ የስልጣን ቦታዎች ላይ ተመድበው ማገልገላቸው ተገልጿል። ባሳለፍነው ሳምንት ቤተ…
Read More