stateofemergency

በኢትዮጵያ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የታሰሩ ሁሉ ከእስር እንዲለቀቁ ኢሰመኮ አሳሰበ

በኢትዮጵያ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የታሰሩ ሁሉ ከእስር እንዲለቀቁ ኢሰመኮ አሳሰበ

በአማራ ክልል ታውጆ የነበረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዛሬ አብቅቷል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ምክንያቱን በአማራ ክልል የተከሰተውን ግጭት ያደረገው እና ለ10 ወራት የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ አዋጅ የጊዜ ገደብ በማለቁ በእስር የቆዩ ሰዎች እንዲለቀቁ አሳስቧል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው በአማራ ክልል በመንግሥት እና በታጣቂ ኃይሎች (በተለምዶ “ፋኖ”) መካከል ከሚካሄደው የትጥቅ ግጭት ጋር ተያይዞ የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ አዋጅ የጊዜ ገደብ በማለቁ በእስር የቆዩ ሰዎች የመልቀቅ ሂደት እንዲቀጥልም አሳስቧል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የነበረው እና ጥር 24 ቀን 2016 ዓ.ም. ለተጨማሪ 4 ወራት የተራዘመው የአስቸኳይ ጊዜ…
Read More
መንግስት በአማራ ክልል የጣለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲያነሳ ተጠየቀ

መንግስት በአማራ ክልል የጣለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲያነሳ ተጠየቀ

የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) በኢትዮጵያ እንደ አዲስ እየተባባሱ የመጡት የሲቪክ ምህዳሩን የሚያጣብቡ ድርጊቶች እንዳሳሰቡት አስታውቋል። የፌደራል መንግሥት ከአንድ ዓመት በፊት የክልል ልዩ ሀይሎችን “መልሼ አደራጃለሁ” የሚል ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ ነበር በአማራ ክልል ግጭት የተከሰተው። ግጭቱ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና የፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተካሄደ ሲሆን ግጭቱ ተባብሶ መቀጠሉን ተከትሎ በአማራ ክልል ለስድስት ወራት የሚዘልቅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ ይታወሳል። ከሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የታወጀው ይህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት የተራዘመ ሲሆን ይህ አዋጅ ሊጠናቀቅ ሶስት ሳምንታት ቀርቶታል። ይኼውም የጸጥታ እና ደህንነት አካላት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ምርመራ የሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን እያዋከቡ ከመሆኑንም ባሻገር በቲያትር እና…
Read More
በአማራ ክልል የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት ተራዘመ

በአማራ ክልል የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት ተራዘመ

በአማራ ክልል የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት ተራዘመ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል ባሳለፍነው ነሀሴ ለስድስት ወራት የታወጀው አስቸኳይ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት ተራዝሟል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ልዩ ስብሰባ በአማራ ክልል የታወጀውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት  አራዝሟል። የምክር ቤቱ አባላት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ዙሪያ አደረጉት በተባለው ውይይት ከዋጁ በሁለት ተቃውሞ በሶሰት ድምፅ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ለአራት ወራት እንዲራዘም መወሰኑ ተገልጿል፡፡ ባሳለፍነው ዓመት ሚያዚያ ወር የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ ለማደራጀት ወስኛለሁ ማለቱን ተከትሎ ነበር በአማራ ክልል ግጭት የተከሰተው፡፡ ይህ ግጭት ቀስ በቀስ እያደገ መጥቶ ወደ ጦርነት የተቀየረ ሲሆን የቀድሞው የክልሉ መንግስት በመደበኛ…
Read More
በአማራ ክልል ከ50 በላይ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ከ50 በላይ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለዉ ጦርነት ምክንያት ክልሉ ከመንግሥት መዋቅር ውጪ ናቸው የተባሉ ወረዳዎች ይፋ ሆነዋል። መንግስት ከቁጥጥር ውጪ የሆኑ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳድር የባንክ ሂሳቦችን እንዳይንቀሳቀሱ እገዳ ጥሏል። ከሰሜን ሸዋ ወረዳዎች ውስጥ ሚዳ ወረሞ፣ መርሃቤቴ፣ አለም ከተማ ፣እነዋሪ፣ መንዝ ቀያ፣ መንዝ ላሎ፣ መንዝ፣ ማማ፣ መንዝ ሞላሌ ከተማ አስተዳድር፣ መንዝ ጌራ፣ ሲያደብር እና ዋዩ፣ እንሳሮ ፣ሞረትና ጅሩ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ናቸው ተብሏል። ከሰሜን ወሎ ወረዳዎች ደግሞ ግዳን ወረዳ ፣እስታይሽ፣ ቡግና እና ሙጃ ወረዳዎች እንዲሁም ከደቡብ ወሎ ደፍሞ ወግዲ ወረዳ፣ ከለላ፣ መካነሰላም ፣ቦረና ፣ አማራ ሳይንት እና ዋድላ ደላንታ ወረዳዎች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ናቸው የተባለ ሲሆን የመንግስት ተቋማት የባንክ ሂሳብ እንዳይንቀሳቀሱ እገዳ…
Read More
አፍሪካ ህብረት በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳሳሰበው ገለጸ

አፍሪካ ህብረት በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳሳሰበው ገለጸ

የአፍሪካ ህብረት ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ አማራ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳሳሰበው አስታውቋል። ህብረቱ በመገለጫው አክሎም የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀማት ጉዳቱን እየተከታተሉት እንደሆነም ገልጿል። ሊቀመንበሩ አክለውም በአማራ ክልል ያለውን ወታደራዊ ፍጥጫ በቅርበት እየተከታተሉት መሆኑንም አስታውቋል። አፍሪካ ህብረት ለኢትዮጵያ ህገመንግስታዊ ስርዓት፣ ሉዓላዊነት እና አንድነት ድጋፍ እንደሚያደርግም ህብረቱ በመግለጫው ላይ ጠቅሷል። ሁሉም የግጭቱ ተሳታፊ አካላት ንጹሀንን ከጉዳት እንዲጠብቁ እና ግጭት እንዲያቆሙ ያሳሰቡት ሊቀመንበሩ ወደ ውይይት እንዲመጡ እና ችግራቸውን እንዲፈቱም አስጠንቅቋል። ሙሳ ፋኪ አክለውም አፍሪካ ህብረት በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ለሚደረጉ ውይይቶች ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። የፌደራል መንግስት ባሳለፍነው ሚያዝያ ወር ላይ የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ አደራጃለሁ በማለቱ በአማራ ክልል ተቃውሞ ገጥሞታል። ይህን ተከትሎም…
Read More
የጠቅላይ ሚንስትሩ የቀድሞ አማካሪ በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ በሀይል እንደማይፈታ ተናገሩ

የጠቅላይ ሚንስትሩ የቀድሞ አማካሪ በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ በሀይል እንደማይፈታ ተናገሩ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሁለት ሳምንት በፊት በሚንስትሮች ምክር ቤት የተወሰነውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጽድቋል። ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት የቀድሞው የጠቅላይ ሚንስትሩ የደህንነት አማካሪ፣ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር እና የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለምክር ቤቱ አባላት ንግግር አድርገዋል። አቶ ገዱ ከሌሎች የምክር ቤቱ አባላት ለየት ባለ መልኩ በአማራ ክልል ስላለው ሁኔታ ባደረጉት ንግግር ከምክር ቤቱ አባላት ተቃውሞ ገጥሟቸው ተቋርጧል። አቶ ገዶ ንግግራቸው እስከተቋረጠበት ጊዜ ድረስ ባደረጉት ንግግር " ብልጽግና መራሹ መንግሥት ራሱ የፖለቲካ ችግር እየፈጠረ ነው" ብለዋል። "ፓርቲው የፈጠረውን የፖለቲካ ችግር ለመፍታት የሚሞክረው ከፖለቲካዊ መፍትሄ ይልቅ ወታደራዊ መፍትሄ ሆኗል" የሚሉት አቶ ገዱ ብልጽግና ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ…
Read More
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል የስድስት ወራት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጸደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል የስድስት ወራት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጸደቀ

የተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የውሳኔ ሀሳብን በአብላጫ ድምጽ በ16 ተቃውሞ እና በ12 ድምጽ ተአቅቦ ማጽደቁ ተገልጿል። የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት በአማራ ክልል እና እንደ አስፈላጊነቱ በሌሎችም ቦታዎች ተግባራዊ ይሆናል የተባለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጽደቁን ምክር ቤቱ በፌስቡክ ገጹ  አስታውቋል። የሚንስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል በትጥቅ የተደገፈ እንቅስቃሴ መኖሩን እና ይህንንም በመደበኛው የህግ ስርአት መቆጣጠር የማይቻልበት ሁኔታ መፈጠሩን በመግለጽ ነበር ለስድስት ወራት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የወሰነው። ምክር ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቦርድ አባላትን እና ሰብሳቢዎችንም መርጧል። በአማራ ክልል፣ በፌደራል መንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተፈጠው ግጭት ንጹሃን ሰዎች እንዲገደሉ ምክንያት መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት…
Read More
በአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታወጀ

በአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታወጀ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉን የጠቅላይ ሚንስቴር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የሕዝብን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በቀረበው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6 /2015 ላይ ነው፡፡ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሚታየውን በትጥቅ የተደገፈ ህገወጥ እንቅስቃሴ በመደበኛ የህግ ማስክበር ስርዓት ለመቆጣጠር ወደ ማይቻልበት ደረጃ የተሸጋገረ በመሆኑ፤ ይህ እንቅስቃሴ የክልሉን ነዋሪ አጠቃላይ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ደረጃ ያወከ እና ህገ መንግስታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ የጣለ በመሆኑ፤ የሕዝብን ሠላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ እንዲሁም ህግ እና ስርዓት ለማስከበር የአስቸኳይ ጊዜ እርምጃዎችን መውሰድ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፣ እንቅስቃሴው በሃገር ደህንነት እና በህዝብ ሰላም…
Read More