Logistics

የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፈ

የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፈ

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ በተያዘው ዓመት ውስጥ 42 ቢሊየን ብር ገቢ አግኝቻለሁ ያለ ሲሆን ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቋል። ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት ደግሞ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን አመልክቷል። የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንዳሉት ኮቪድ 19፣ የዩክሬንና ሩሲያ ጦርነት፣ የሀገር ውስጥ ፀጥታ ችግርና ሌሎች ችግሮች በድርጅቱ ስራዎች ላይ ተፅዕኖ ነበራቸው። በበጀት ዓመቱ ከውጭ ወደ አገር ውስጥ ከተጓጓዘው 7 ነጥብ 4 ሚሊየን ቶን እቃ ውስጥ 34 በመቶውን የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ማጓጓዙን ገልጸዋል። በመርከብ የወጪ ጭነትና ጥቅል ጭነት አገልግሎት በእቅዱ ልክ መፈፀሙን ጠቅሰው፣ በብረት ማጓጓዝ ረገድ ግን ዝቅተኛ…
Read More
አቶ ሮባ መገርሳ ከሀላፊነት ተነሱ

አቶ ሮባ መገርሳ ከሀላፊነት ተነሱ

የኢትዮጵያ ባህር ሎጅስቲክስ አገልግሎትን ላለፉት አምስት ዓመታት በሀላፊነት የመሩት አቶ ሮባ መገርሳ ከሀላፊነት ተነስተዋል። በዚህ ተቋም ከባለሙያነት ጀምሮ ያገለገሉት አቶ ሮባ ለምን ከሀላፊነት እንደተነሱ ይፋ አልተደረገም። በአቶ ሮባ ቦታም በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) ከትናንት መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ መሾማቸውን ኢትዮ ነጋሪ ከተቋሙ የኮሙንኬሽን ሀላፊ አቶ ደምሰው በንቲ አረጋግጣለች። አዲሱ ሀላፊ ከዚህ በፊት በኦሮሚያ ክልል ከወረዳ እስከ ፌደራል ተቋማት በተለያዩ የሀላፊነት ቦታዎች ላይ መስራታቸው ተገልጿል።
Read More