Ethiopiamaritime

የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፈ

የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፈ

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ በተያዘው ዓመት ውስጥ 42 ቢሊየን ብር ገቢ አግኝቻለሁ ያለ ሲሆን ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቋል። ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት ደግሞ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን አመልክቷል። የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንዳሉት ኮቪድ 19፣ የዩክሬንና ሩሲያ ጦርነት፣ የሀገር ውስጥ ፀጥታ ችግርና ሌሎች ችግሮች በድርጅቱ ስራዎች ላይ ተፅዕኖ ነበራቸው። በበጀት ዓመቱ ከውጭ ወደ አገር ውስጥ ከተጓጓዘው 7 ነጥብ 4 ሚሊየን ቶን እቃ ውስጥ 34 በመቶውን የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ማጓጓዙን ገልጸዋል። በመርከብ የወጪ ጭነትና ጥቅል ጭነት አገልግሎት በእቅዱ ልክ መፈፀሙን ጠቅሰው፣ በብረት ማጓጓዝ ረገድ ግን ዝቅተኛ…
Read More
ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች

ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች

ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ በቅርቡ ባህር ዳር እና ሀዋሳ የተሰኙ ሁለት መርከቦች ለኪሳራ ዳርገውኛል በሚል መሸጡ ይታወሳል። በተሸጡት ሁለት መርከቦች ምትክም አባይ የተሰኘች አዲስ መርከብ ከቻይና መግዛቱን አስታውቋል። አዲሷ መርከብም በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ታሪክ በግዙፍነቷ አቻ የላትም የተባለ ሲሆን መርከቧ በኢትዮጵያ እጅ መግባቷን ድርጅቱ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ድርጅት በ3 ሺህ ቶን የመጫን አቅም ባላቸው መርከቦች ስራውን መጀመሩ ይታወሳል። ኢትዮጵያ የተረከበቻት አባይ የተሰኘችው አዲሷ መርከብ 63 ሺህ 229 ቶን የመጫን አቅም አላት ተብሏል። በቻይናው ያንግዡ ዳያንግ ሺፕ ቢዩልዲንግ የተገነባችው ይህች መርከብ 200 ሜትር ርዝመት እንዳላትም ተገልጿል። ይሁንና…
Read More