Jews

በእስራኤልና ሃማስ ጦርነት ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያውያን መጎዳታቸው ተገለጸ

በእስራኤልና ሃማስ ጦርነት ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያውያን መጎዳታቸው ተገለጸ

ሃማስ በእስራኤል ላይ መጠነ ሰፊ  ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ በሀገሪቱ የሚገኙ ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያዉያን ሰለባ መሆናቸዉን በኢትዮጵያ እስራኤል ኤምባሲ  አስታዉቋል፡፡ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለሊ አደማሱ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት በወቅታዊ የጉዳቱን መጠን አሁን ላይ መግለጽ ባይቻልም ከተጎጂዎች መካከል ግን ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያዉያን እንደሚኖሩ ተናግረዋል፡፡ በጥቃቱ ከ700 በላይ እስራኤላዉያን መሞታቸዉን አምባሳደር አለሊ አስታዉቀዋል፡፡ በተጨማሪም ከ2 ሺህ በላይ ዜጎች ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዉ በሞት አፋፍ ላይ እንደሚገኙ አምባሳደሩ ተናግረዋል፡፡ አሁን ላይ የእስራኤል ጦር ኃይል የሃማስን ጥቃት በመመከት  ጎን ለጎን የሞቱ ዜጎችን እየቀበረ እንደሚገኝ ኤምባሲዉ አስታዉቋል፡፡ ሃማስ የጀመረዉ ጥቃት በቀላሉ የሚታልፍ እንዳልሆነም አምባሳደር አለሊ ገልጸዋል፡፡ እስራኤል አንድ መቶ ሺህ ወታደሮቿን ወደ ጋዛ ማሰመራቷንም አስታዉቃለች፡፡…
Read More
እስራኤል ሁከት የፈጠሩ ኤርትራዊያንን ለማባረር ወሰነች

እስራኤል ሁከት የፈጠሩ ኤርትራዊያንን ለማባረር ወሰነች

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በቴላቪቭ በሃይለኛ ግጭት ውስጥ የተሳተፉ ኤርትራውያን በአስቸኳይ እንዲባረሩ እንደሚፈልጉ ገልፀዋል። የሀገሪቱን አፍሪካውያን ስደተኞች በሙሉ ለማስወገድ እቅድ ማውጣታቸውን አስታውቀዋል። ይህንን አስተያየት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰጡት በደቡባዊ ቴል አቪቭ በኤርትራ ተቀናቃኝ ቡድኖች መካከል በነበረ ደም አፋሳሽ ግጭት በርካታ ሰዎች ላይ ጉዳት ከደረሰ  ከአንድ ቀን በኋላ ነበር። ኔታንያሁ የተከሰተውን ሁከት ተከትሎ በትላንትናው እለት በተጠራው ልዩ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ “በሁከት ፈጣሪዎች ላይ ከባድ እርምጃዎችን እንፈልጋለን ፣ የተሳተፉትን ወዲያውኑ ወደ መጡበት መመለስ እንፈልጋለን” ብለዋል ። ሚኒስትሮቹ “ሌሎች ህገወጥ ሰርጎ ገቦችን ለማስወገድ” እቅድ እንዲያቀርቡላቸው የጠየቁ ሲሆን ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ስደተኞቹን ለቀው እንዲወጡ ለማስገደድ የታቀዱ አንዳንድ እርምጃዎችን መተላለፉን በንግግራቸው አስታውቀዋል። በአለም አቀፍ ህግ…
Read More
እስራኤል የኢትዮጵያን ሁኔታ የሚከታተል የጦር መሪ ሾመች

እስራኤል የኢትዮጵያን ሁኔታ የሚከታተል የጦር መሪ ሾመች

ብርጋዴር ጀነራል ሀርል ክንፎ በኢትዮጵያ ያሉ ቤተ እስራኤላዊያንን ጉዳይ እንዲከታተሉ መሾማቸው ተገልጿል። እንደ ጀሩሳሌም ፖስት ዘገባ ከሆነ የእስራኤል መንግሥት በኢትዮጵያ የሚገኙ ቤተ እስራኤላዊያን የሚያነሱትን ቅሬታ የሚከታተልና የመፍትሔ ሀሳብ የሚያቀርብ ወታደራዊ መሪ መሾሙ ተገልጿል። ጀነራሉ የእስራኤል አሊያስ እና የውህደት ሚኒስቴር በኩል እንደተሾሙ የተገለጹ ሲሆን ኢትዮጵያን በተመለከተ የእስራኤልን ወቅታዊ የስደት ፖሊሲ የሚገመግም ቡድን እንዲያዋቅሩም ተጨማሪ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል ተብሏል። ከአገሪቱ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ይሁንታ በመጠባበቅ ላይ ያሉት ጀነራሉ የጥናት ቡድኑ በአዲስ አበባ እና በጎንደር ወደ እስራኤል ለማቅናት በሚጠባበቁ ቤተ እስራኤላውያንን መርዳት ዋነኛ ስራቸው እንደሚሆንም በዘገባው ላይ ተጠቅሷል። ብርጋዴር ጄኔራል ሃርል ከዚህ ቀደም በእስራኤል ቁልፍ የስልጣን ቦታዎች ላይ ተመድበው ማገልገላቸው ተገልጿል። ባሳለፍነው ሳምንት ቤተ…
Read More
እስራኤል ከአማራ ክልል 200 ዜጎቿን ከኢትዮጵያ አጓጓዘች

እስራኤል ከአማራ ክልል 200 ዜጎቿን ከኢትዮጵያ አጓጓዘች

እስራኤል ከአማራ ክልል 200 የሚሆኑ ዜጎቿንና አይሁዳውያንን ማስወጣቷን አስታወቀች። የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚንስቴርና የጠቅላይ ሚንስቴር ጽ/ቤት በጋራ ባወጡት መግለጫ በክልሉ በተነሳው ግጭት 174 እስራኤላዊያንና ወደ ሀገሪቱ ለመግባት ብቁ የሆኑ ቤተ-እስራኤላዊያን ከጎንደር እንዲወጡ ተደርጓል። ሌሎች 30 የሚሆኑ ዜጎች ደግሞ ከባህር ዳር መውጣታቸው ተነግሯል።  በአራት በረራዎች ከአማራ ክልል እንዲወጡ የተደረጉት ዜጎች አዲስ አበባ ደርሰዋል ተብሏል። ከአዲስ አበባም ወደ እስራኤል ያቀናሉ ተብሎ ይጠበቃል። የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኢላይ ኮን እስራኤላዊያኑ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እስኪወስኑ ድረስ በአዲስ አበባ እንደሚቆዩ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ መቆየትም እንደሚችሉም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ እስራኤል ዜጎቿን የትም ይሁኑ የት ጥበቃ እንደምታደርግላቸው መናገራቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኸን ዘግቧል። ጠቅላይ ሚንስትሩ "አጭር፣ ኮሽታ…
Read More