Telaviv

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስራኤል አቋርጦት የነበረውን በረራ እንደሚጀምር ገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስራኤል አቋርጦት የነበረውን በረራ እንደሚጀምር ገለጸ፡፡

ሃማስ በእስራኤል ላይ ድንገተኛ እና ያለተጠበቀ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የተቀሰቀሰው ጦርነት ከተጀመረ 47ኛ ቀኑን ይዟል። ከሁለቱም ወገን 15 ሺህ ገደማ ሰዎች የተገደሉበት ይህ ጦርነት እንዲቆም በርካቶች ሲያሳስቡ ቢቆዩም ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ በጦርነቱ ምክንያት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በርካታ የዓለማችን አየር መንገዶች ወደ እስራኤል ሲያደርጉት የነበረውን በረራ አቋርጠው ቆይተዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከህዳር 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን በረራ ዳግም እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ አየር መንገዱ አክሎም በሳምንት አምስት ቀናት ከአዲስ አበባ-ቴልአቪቭ ከተማ የቀጥታ በረራውን እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡ የደርሶ መልስ ትራንስፖርት አገልግሎቱን በበረራ መስመር ኢት 404 እና 405 አውሮፕላኖቹ  እንደሚሰጥ የገለጸው አየር መንገዱ ሁሉንም የሳምንቱ ቀናት…
Read More
እስራኤል ከአማራ ክልል 200 ዜጎቿን ከኢትዮጵያ አጓጓዘች

እስራኤል ከአማራ ክልል 200 ዜጎቿን ከኢትዮጵያ አጓጓዘች

እስራኤል ከአማራ ክልል 200 የሚሆኑ ዜጎቿንና አይሁዳውያንን ማስወጣቷን አስታወቀች። የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚንስቴርና የጠቅላይ ሚንስቴር ጽ/ቤት በጋራ ባወጡት መግለጫ በክልሉ በተነሳው ግጭት 174 እስራኤላዊያንና ወደ ሀገሪቱ ለመግባት ብቁ የሆኑ ቤተ-እስራኤላዊያን ከጎንደር እንዲወጡ ተደርጓል። ሌሎች 30 የሚሆኑ ዜጎች ደግሞ ከባህር ዳር መውጣታቸው ተነግሯል።  በአራት በረራዎች ከአማራ ክልል እንዲወጡ የተደረጉት ዜጎች አዲስ አበባ ደርሰዋል ተብሏል። ከአዲስ አበባም ወደ እስራኤል ያቀናሉ ተብሎ ይጠበቃል። የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኢላይ ኮን እስራኤላዊያኑ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እስኪወስኑ ድረስ በአዲስ አበባ እንደሚቆዩ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ መቆየትም እንደሚችሉም ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ እስራኤል ዜጎቿን የትም ይሁኑ የት ጥበቃ እንደምታደርግላቸው መናገራቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኸን ዘግቧል። ጠቅላይ ሚንስትሩ "አጭር፣ ኮሽታ…
Read More
እስራኤል ሁለት ሺህ ቤተ እስራኤላዊያንን ከኢትዮጵያ ልትወስድ መሆኗን ገለጸች

እስራኤል ሁለት ሺህ ቤተ እስራኤላዊያንን ከኢትዮጵያ ልትወስድ መሆኗን ገለጸች

የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያኹ ለመንግስታቸዉ ከኢትዮጵያዉያን ቤተ እስራኤላውያን ማህበረሰብ ጋር ያላቸዉን ግንኙነት ማጠናከር ባለባቸዉ ጉዳዮች ላይ ያቀረቡት እቅድ ጸድቋል። በዚህ እቅድ መሰረትም 2 ሺህ ቤተእስራኤላውያንን ወደ ቴልአቪቭ ለመዉሰድ ማቀዳቸዉን ጀረሰላም ፖስት ዘግቧል። እ.ኤ.አ በ 2015 የእስራኤል መንግስት 9 ሺህ የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እስራኤል መግባት የሚፈልጉ ቤተ እስራኤላውያንን ጥያቄ ከተቀበለ በኋላ ባገጠመዉ የበጀት እጥረት ማጓጓዝ ሳይችል መቅረቱ ተዘግቧል። በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀረበ የተባለዉ እቅድ ኢትዮጵያዊ ቤተ እስራኤላዊያንን ለማጓጓዝ 66 ሚሊዮን ዶላር በጀት ተይዞለታልም ተብሏል። የሀገሪቱ መንግስት በእስራል ከሚገኙ ከ 160 ሺህ በላይ ቤተ እስራኤላውያን ዜጎች ጋር ያለዉን ግንኙነት  በማጠናከር በተለይም ወደ ሀገሪቱ የጦር ሀይል ለማካተት እቅድ እንዳለዉ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል። በተጨማሪም በእስራኤላውያን…
Read More