DashenBank

ዳሸን ባንክ ከሁለት የአውሮፓ ባንኮች 40 ሚሊዮን ዶላር ብድር አገኘ

ዳሸን ባንክ ከሁለት የአውሮፓ ባንኮች 40 ሚሊዮን ዶላር ብድር አገኘ

ዳሸን ባንክ ከእንግሊዝ እና ኔዘርላንድ ባንኮች 40 ሚሊዮን ዶላር ብድር አገኘ የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት (ቢ አይ አይ) እና የኔዘርላንድ የሥራ ፈጠራና ልማት ባንክ የሆነው (ኤፍ ኤም ኦ) እያንዳንዳቸው 20 ሚሊየን ዶላር በድምሩ 40 ሚሊየን ዶላር ብድር ለዳሸን ባንክ ማቅረባቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ የብድር አቅርቦቱ ኢትዮጵያ ለውጪ ገበያ የምታቀርበውን የግብርና ምርት ለማሳደግ እና በእጅጉ አስፈላጊ የሆነውን የውጪ ምንዛሬ አቅርቦት ለማሻሻል እንደሚያስችል ተመላክቷል፡፡ ቢ አይ አይ እና ኤፍኤምኦ ለዳሸን ባንክ ያቀረቡት ገንዘብ በኢትዮጵያ 80 በመቶ የህብረተሰብ ክፍል በተሰማራበት፣ ለጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት 39 በመቶ ድርሻ ላለው እና ለወጪ ንግዱ 90 በመቶ አስተዋጽኦ ለሚያበረክተው የግብርና ዘርፍ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረውም ታምኖበታል፡፡ የቀረበው ብድር ባንኩ…
Read More
ዳሸን ባንክ ደንበኞቹ ከየትኛውም ሀገር ሆነው ገንዘባቸውን ማንቀሳቀስ የሚያስችል ቴክኖሎጂ አስጀመረ

ዳሸን ባንክ ደንበኞቹ ከየትኛውም ሀገር ሆነው ገንዘባቸውን ማንቀሳቀስ የሚያስችል ቴክኖሎጂ አስጀመረ

ዳሸን ባንክ እና ማስተር ካርድ በጋራ በመተባበር "ቨርቹዋል የቅድመ ክፍያ ካርድ" የተሰኘ አገልግሎት በይፉ አስተዋውቀዋል፡፡ ካርዱ ከተለደው እና በሥም ከሚታተመው የፕላስቲክ ካርድ የተለየ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ደንበኞች ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ሆነው ገንዘባቸውን መጠቀምና ማንቀሳቀስ የሚችሉበት አማራጭ ነው ተብሏል። የዳሸን ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ እንዳሉት "ዳሸን ባንክ ይህን በአይነቱ የተለየ ካርድ ማስተዋወቁ፤ ባንኩ ለደንበኞቹ ቀላል፣ ምቹና አስተማማኝ የፋይናስ አገልግሎቶችን ይበልጥ ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል" ብለዋል፡፡ ዳሽን ባንክ ከዚህ ቀደም "የውጪ ምንዛሬ ሂሳብ" ላላቸው ደንበኞቹ ብቻ የሚያገለግል ካርድ በሥራ ላይ ማዋሉን ያስታወሱት ፕሬዝዳንቱ አዲስ የተዋወቀው “ቨርቹዋል የቅድመ ክፍያ ካርድ” በአጠቃላይ ለአለም ዓቀፍ ተጓዦች ታስቦና ከፍተኛ የደህንነት መጠበቂያ ተደርጎለት በአማራጭነት…
Read More
በባለስልጣን ጠባቂ ወታደር የተጠለፈችው የባንክ ሰራተኛ እስካሁን ያለችበት አልታወቀም

በባለስልጣን ጠባቂ ወታደር የተጠለፈችው የባንክ ሰራተኛ እስካሁን ያለችበት አልታወቀም

የዳሽን ባንክ ሐዋሳ ቅርንጫፍ ባለሙያ የሆነችው ፀጋ በላቸው በሐዋሳ ከንቲባ ጠባቂ ኮንስታብል የኋላመብራት ወልደማርያም መጠለፏ ተገልጿል። የሲዳማ እና ደቡብ ክልል ዋና ከተማ በሆነችው ሀዋሳ ከተማ ይህ መፈጸሙ ብዙዎችን ያስደነገጠ ድርጊት ሆኗል። ባለሙያዋ በሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ፀጋዬ ቱኬ የግል ጠባቂ ኮንስታብል የኋላመብራት ወ/ማሪያም ተጠልፋ ከተወሰደች ከሳምንት በላይ ሆኗታል። የተጎጂዋ ቤተሰቦች እንዳሉት የግል ተበዳይ በቤተ ክርስቲያን ደንብ መሰረት የጋብቻ ትምህርት ከወደፊት የትዳር አጋሯ ጋር ተምረው በማጠናቀቅ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ ለመጋባት ቀን ቆርጠው የቤት ዕቃዎችን በማሟላት ላይ ነበሩ። ይሁን እንጂ ጥቃት አድርሷል በሚል በፖሊስ የሚፈለገው ተጠርጣሪ የግል ተበዳይን በተደጋጋሚ ይዝትባት እና ያስፈራራት እንደነበር ቤተሰቦቿ ተናግረዋል። የግል ተበዳይ ቤተሰቦች ፀጋ ያለችበትን ባለማወቃቸው ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ…
Read More