ኢኮኖሚ

ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ የገንዘብ ድጋፍ ማረጋገጫ አገኘች

ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ የገንዘብ ድጋፍ ማረጋገጫ አገኘች

ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ እን አይኤምኤፍ ጋር ስታደርገው የነበረው ውይይት ተጠናቋል። የኢትዮጵያ የፋይናንስ ልዑክ ከዓለም ባንክ እና ከዓለም አቀፉ የገንዘባ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ሃላፊዎች ጋር በዋሽንግተን ለአንድ ሳምንት ሲያደርግ የነበረውን ውይይት አጠናቅቋል፡፡ በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሽ በቀለ በትዊተር ገጻቸው እንዳስታወቁት በገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ እና በብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ የተመራው ልዑክ ከዓለም ባንክ እና ከዓለማቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ዳይሬክተሮች ጋር ሲያደርግ የነበረው ውይይት ተጠናቋል፡፡ የፋይናንስ ልዑኩ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አይ ኤም ኤፍ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂየቫ እና ልዑካቸው ጋር ምክክር ማድረጋቸውን እና ለአንድ ሳምንት የቆየውን ውይይት መጠናቀቁን አንስተዋል፡፡ የተደረገው ውይይት ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋትን የልማትና ሰብዓዊ  ድጋፍ ለማግኘት…
Read More
በደብረ ብርሃን ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑ ተገለጸ

በደብረ ብርሃን ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑ ተገለጸ

የደብረብርሃን ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሪት መሰረት መንገሻ እንደገለጹት ከትላንት ጀምሮ መርዝ ተጨምሮበት ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ተቋማቸው አንዱ ተግባሩ የሚያመርተውን ውሃ ጥራት አረጋግጦ ለተጠቃሚዎች ማሰራጨት ሃላፊነታቸው በመሆኑን ባለሙያዎች እሁድ ቅዳሜን እና የበዓላትን ቀናት ጭምር አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡ የውሃ ማጠራቀሚያ ጋኖች ታጥረው የሚጠበቁ ከመሆኑም በላይ ሁል ጊዜ በባለሙያ ክትትል እየተደረገላቸው ውሃው በባለሙያ ጥራቱ ተረጋግጦ ለደንበኞች እንደሚሰራጭ አረጋግጠዋል፡፡ የፀጥታ ችግር ሲከሰት ደግሞ በልዩ ሁኔታ ጥበቃና ክትትል እንደሚደረግላቸው ጠቁመዋል፡፡ ችግር ካጋጠመም ውሃው እንደማይለቀቅ ጠቅሰው ህብረተሰቡ የውሃ ተቋሙ የሚያደርገውን ጥንቃቄ በአግባቡ ተረድቶ በአሉባልታ ወሬ እንዳይረበሽ መክረዋል፡ ውሃው 100 ፐርሰንት ንጹህ መሆኑን ስራ አስኪያጇ መልዕክታቸውን…
Read More
ግብጽ የህዳሴው ግድብን ዓለም አቀፋዊ ከማድረግ እንድትታቀብ ኢትዮጵያ አሳሰበች

ግብጽ የህዳሴው ግድብን ዓለም አቀፋዊ ከማድረግ እንድትታቀብ ኢትዮጵያ አሳሰበች

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት ግብጽ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ተደጋጋሚ መግለጫዎችን እያወጣች ነው። መግለጫዎቹ ኢትዮጵያ በቀጣይ ክረምት ወራት ግድቡ ውሀ እንዲይዝ የተናጠል ውሳኔ እንዳትወስን የሚያሳስቡ ናቸው። በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ከጋዜጠኞች ለቀረበው ጥያቄ "ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ ውሀ አሞላል ዙሪያ ማንንም የማስፈቀድ ግዴታ የለባትም" ብለዋል። ታላቁ የህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ ግዛት እና ሀብት እየተገነባ ያለ ፕሮጀክት ነው የሚሉት አምባሳደር መለስ በእቅዳችን እና በፕሮግራማችን እንመራለን ሲሉም አክለዋል። የግብጽ ሰሞንኛ ተደጋጋሚ መግለጫ የህዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር ውሀ መመሙያ ጊዜ እየተቃረበ መምጣቱን ተከትሎ ጉዳዩን ዓለም አቀፋዊ ለማድረግ ያለመ እንደሆነም ቃል አቀባዩ…
Read More
እነ ዶክተር ሙሉቀን ሀብቱ ከተከሰሱበት የሙስና ወንጀል በነጻ ተሰናበቱ

እነ ዶክተር ሙሉቀን ሀብቱ ከተከሰሱበት የሙስና ወንጀል በነጻ ተሰናበቱ

ዶ/ር ሙሉቀን ሐብቱን ጨምሮ ከጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ክስ የተመሰረተባቸው አምስት ግለሰቦች በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነጻ ተባሉ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያና ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉቀን ሐብቱን ጨምሮ ከጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው አምስት ግለሰቦች በነጻ አሰናብቷቸዋል፡፡  ፍርድ ቤቱ ብይኑን የሰጠው ዛሬ ረቡዕ ሚያዚያ 4፤ 2015 በዋለው ችሎት ነው፡፡  በዚሁ መዝገብ ክስ ከቀረበባቸው ግለሰቦች መካከል አንድ ተከሳሽ በሌሉበት ጥፋተኛ ሲባሉ፤ ቀሪ አምስት ተከሳሾች ደግሞ የተከሰሱበት ድንጋጌ ተቀይሮ እንዲከላከሉ በፍርድ ቤቱ በይኗል። ችሎቱ አምስት ተከሳሾችን በነጻ ያሰናበተው፤ “ዐቃቤ ህግ ባቀረበው የሰው…
Read More
ግዙፉ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገለጸ

ግዙፉ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገለጸ

በቻይና በሲሚንቶ ዘርፍ የተሰማራው ግዙፉ ሲኖማ ዓለም አቀፍ ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገልጿል። በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው የሲኖማ ዓለም አቀፍ ኩባንያ ሊቀመንበር እና የሲኤንቢኤም ተቋም ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ሚስተር ሉ ያን እና የሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር ተወያይተዋል። ኩባንያው በኢትዮጵያ ኢንቨስት በሚደረግበት ዙሪያ ቤጂንግ በሚገኘው የኩባንያው ዋና ጽ/ቤት ተገኝተው ውይይት አድርገዋል። አምባሳደር ተፈራ በውይይቱ ወቅት ኩባንያው በኢትዮጵያ ባሉት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ከዲዛይን ጀምሮ በግንባታ ረገድ ላበረከተው አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበው፣ በኢትዮጵያ ካለው የግንባታ ስፋት አንጻር የሲሚንቶ ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል። አምባሳደር ተፈራ አያይዘውም፣ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ከፍተኛ የሆነ የሲሚንቶ ፍላጎት ግምት ውስጥ በማስገባት በኢንቨስትመንቱ ዘርፍ ቢሰማራ የጋራ ተጠቃሚነቱ ሰፊ መሆኑን ገልጸዋል።…
Read More
የኢትዮጵያ ትልቁ ባንክ ከቻይናው የቴክስታይል ኩባንያ ጋር ስምምነት ተፈራረመ

የኢትዮጵያ ትልቁ ባንክ ከቻይናው የቴክስታይል ኩባንያ ጋር ስምምነት ተፈራረመ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሠራተኞቹ የደንብ ልብስ ከሚያቀርብ የቻይና ቴክስታይል ኩባንያ ጋር ተፈራርሟል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሠራተኞቹ የደንብ ልብስ አቅርቦት ከቻይናው ጂያንግሱ ሰንሻይን ግሩፕ ጋር መፈራረሙን አስታውቋል። የንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቤ ሳኖ ጥራት ያለው የደንብ ልብስ ለሠራተኞች እንዲቀርብ የሚያስችል ውይይት ከጂያንግሱ ሰንሻይን ግሩፕ ተወካዮች ጋር መወያየታቸው ተመላክቷል፡፡ ለደንብ ልብስ አቅርቦቱ ባንኩ ከፍተኛ ወጪ በመመደብ ለአብዛኛው ሠራተኛ ወጪውን የሸፈነ ሲሆን፣ በመካከለኛና ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ የባንኩ ሠራተኞች እንዲሁም የሥራ ኃላፊዎች ደግሞ የተወሰነ ወጪ ተጋርተው የሚቀርብ መሆኑን አቶ አቤ ገልፀዋል፡፡ የጂያንግሱ ሰንሻይን ግሩፕ በኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚ/ር ጋዊ ቻንሁሀ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች ደንብ ልብስ ተቋማቸው በኢትዮጵያ ቅርንጫፉ ከሚሰራቸው አቅርቦቶች ትልቁ…
Read More
ሸራተን ሆቴል በጅማ ከተማ ባለ አምስት ኮኮብ ሆቴል ሊገነባ ነው

ሸራተን ሆቴል በጅማ ከተማ ባለ አምስት ኮኮብ ሆቴል ሊገነባ ነው

በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር ያለው ሸራተን ሆቴል በ ጅማ ከተማ በፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ደረጃ ባለ አምስት ኮከብ ኢንተርናሽናል ሆቴል ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀምጧል:: የግንባታ መሰረተ ድንጋዩን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ አስቀምጠዋል፡፡ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከዚህ በፊት ጅማ ከተማ ኖክ ማደያ አካባቢ ለመገንባት አቅዶ የነበረውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ዘመናዊ ሆቴል ወደ ከተማዋ መግቢያ እንዲዛወር ተደርጓል። ከዚህ በፊት ሆቴሉ ሊገነባበት የነበረው ቦታ ላይም ዘመናዊ የገበያ ማዕከል እንደሚገነባም የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ኩባንያ አቶ ጀማል አህመድ ተናግረዋል። የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በበኩላቸው ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በኦሮሚያ ክልል ሰፊ…
Read More
ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ በመሸመት ቀዳሚ አገር ሆነች

ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ በመሸመት ቀዳሚ አገር ሆነች

ኬንያ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል በመሸመት ቀዳሚ መሆኗ የተገለጸ ሲሆን፤ በተለይ ባለፈው ጥር ወር ያስገባቸው የኃይል መጠን በታሪክ ከፍተኛው ነው ተብሏል፡፡ ይህ የሆነውም በምስራቅ አፍሪካ ባጋጠመው አስከፊ ድርቅ ምክንያት የኃይል ማመንጫ ግድቦች ውሃቸው በመድረቁ ምክንያት መሆኑ ተነግሯል፡፡ ከኬንያ ስታትስቲክስ ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፤ አገሪቱ ባለፈው ጥር ወር 68 ነጥብ 48 ሚሊዮን ኪሎዋት ኤሌክትሪክ ኃይል አስገብታለች፡፡ ኹለቱ አገራት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ የኤሌክትሪክ ኃይል በቅናሽ ለመገበያየት ከተስማሙ በኋላ፤ ኬንያ 39 ሚሊዮን ዩኒት ኃይል ከኢትዮጵያ ማስገባቷ ተነግሯል፡፡ በዚህም አገሪቷ በርካሽ ዋጋ ኃይል ለማስገባት ከተስማማች በኋላ ጥር ላይ 200 ሜጋዋት የኤሌክትርክ ኃይል ከኢትዮጵያ ማስገባቷ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህም የኃይል አቅርቦቱን ለማረጋጋት እንዳስቻላት ተጠቁሟል፡፡ ኬንያ…
Read More
ኢትዮጵያ በህገ ወጥ ማዕድን ማውጣት ስራ ተሰማርተው የተገኙ 90 የውጭ ዜጎችን አሰረች

ኢትዮጵያ በህገ ወጥ ማዕድን ማውጣት ስራ ተሰማርተው የተገኙ 90 የውጭ ዜጎችን አሰረች

የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ያላቸው ዜጎች በኢትዮጵያ በማእድን ማውጣት ስራ ተሰማርተው ተገኝተዋል ተብሏል፡፡ በጋምቤላ ክልል በህገ ወጥ መንገድ ወርቅን ጨምሮ ማእድን ማውጣት ሰራ ላይ የተሰማሩ 45 የውጭ ሀገራት ዜጎች መያዛቸውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገልጿል። የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ደኤታ ሰላማዊት ካሳ በሰጡት መግለጫ በክልሉ 3 ኢትዮጵያውያንም ተይዘዋል ብለዋል፡፡ በተመሳሳይ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል 47 የውጭ ዜጎች ወርቅን ጨምሮ በማእድን ማውጣት ስራ ላይ ተሰማርተው ሲያዙ 9 የግል ማህበራትና 7 ኢትዮጵያውያንም በቁጥጥር ስር ውለዋል ተብላል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ከሰሞኑ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዳሉት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በህገ ወጥ ማእድን ንግድ መታወኩን ተናግረው ነበር። እነዚህን ህገወጥ የማእድን አዘዋዋሪዎች ለመቆጣጠር የጸጥታ ሀይል እናሰማራለን ሲሉ ለምክር ቤቱ…
Read More
የሩሲያ መኪና አምራች ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስት ሊያደርጉ መሆኑን ገለጹ

የሩሲያ መኪና አምራች ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስት ሊያደርጉ መሆኑን ገለጹ

የሩሲያ  የመኪና አምራች ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ጉብኝት በማድረግ ላይ ሲሆኑ በድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጠና ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ ከሩሲያ የላዳ እና ጋዝ ግሩፕ መኪና አምራች ኩባንያዎች የመጡ ተወካዮች ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ሰለሞን ጋር ተወያይተዋል፡፡ ለተወካዮቹ  በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ፣ ስለዘርፉ ማበረታቻዎች እንዲሁም በአፍሪካ ግንባር ቀደም ስለሆነው የድሬዳዋ የነጻ ንግድ ቀጠና አጠቃላይ ገለጻ ተደረገላቸዋል፡፡ የመኪና አምራች ኩባንያ ኃላፊዎቹ ከድሬዳዋ በተጨማሪ የቦሌ ለሚ እና ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን የስራ እንቅስቃሴና የምርት ሂደት ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡ ኩባንያዎቹ በአውሮፓ፣ በደቡብ አሜሪካና የአፍሪካ ገበያዎች ለጤና ተቋማት፣ ለፀጥታ አካላት፣ ለጭነት አገልግሎት እንዲሁም ለግልና ለህዝብ ትራንስፖርት ዘርፍ…
Read More