ኢኮኖሚ

ከ10 ሺህ በላይ የሚሳተፉበት ሀገር አቀፍ የወጣቶች ፌስቲቫል ተዘጋጀ

ከ10 ሺህ በላይ የሚሳተፉበት ሀገር አቀፍ የወጣቶች ፌስቲቫል ተዘጋጀ

(ኢትዮ ነጋሪ፣ መጋቢት 28 ቀን 2015 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ) “ዛሬን በንቃት፣ ነገን በስኬት” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀው ይህ ሃገር-አቀፍ የወጣቶች ፌስቲቫል ከሚያዚያ 21 እሰከ 22 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል ተበሏል፡፡ ፌስቲቫሉ በአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅተ የገንዘብ ድጋፍ በሚተገበረው ከፍታ የተቀናጀ የወጣቶች ፕሮግራም በኩል የሚዘጋጅ ሲሆን አምሬፍ ሄልዝ አፍሪካ ከአጋሮቹ እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ፌስቲቫሉን እንደሚመራ ተገልጿል፡፡ የከፍታ የተቀናጀ የወጣቶች ፕሮግራም ቺፍ ኦፍ ፓርቲ አቶ ቻላቸው ጥሩነህ እንዳሉት ወጣቶችን በተለያዩ መስኮች ብቁ ማድረግ የዚህ ፌስቲቫል ዋና አላማ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ፌስቲቫሉ የወጣቶች ስኬት ዕውቅና የሚሰጥበት፣ ከተለያዩ ዘርፎች የመጡ ወጣቶች ልምድ የሚለዋወጡበት፣ እንዲሁም ለበለጠ ስኬት…
Read More
ኢትዮጵያ በ10 ዓመት ከ44 ቢሊዮን ዶላር በላይ ሀብት ከሀገር እንደሸሸባት ተገለጸ

ኢትዮጵያ በ10 ዓመት ከ44 ቢሊዮን ዶላር በላይ ሀብት ከሀገር እንደሸሸባት ተገለጸ

በ10 ዓመቱ ወደ ውጪ ሸሽቷል የተባለው ሀብት ከባለፈው 44 ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ10 ዓመቱ እንደሚበልጥ የጥናት ወሬውን የማክሮ ኢኮኖሚ ተንታኝና ተመራማሪው ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ ለሸገር ሬድዮ ተናግረዋል፡፡ ተመራማሪው በከተማው ውስጥ ከመደበኛው ሥርዓት ውጪም ከፍተኛ ዶላር እንደሚገላበጥ አስረድተዋል፡፡ ኢትዮጵያ በ10 ዓመት ውስጥ ብቻ 45 ቢሊየን ዶላር በሚዘገንን ሁኔታ ከሀገር ወጥቷል ብለዋል ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ፡፡ በቅርቡ 10 ዓመት የወጣው የውጭ ምንዛሪ ከባለፈው 44 አመት እንደሚልቅ ተሰምቷል፡፡ የማክሮ ኢኮኖሚ ተመራማሪው በ44 ዓመት ውስጥ ከኢትዮጵያ የሸሸው ሀብት 31 ቢሊየን ዶላር መሆኑን በጥናት ተረጋግጦ መታተሙን ተናግረዋል፡፡ የሀብት ማሸሻ ጥድፊያው በጣም አስደንጋጭ ነው የተባለ ሲሆን ለዚህ የዶላርና የገንዘብ ፍልሰት ወይም ካፒታል ፍላይት ዋነኛው ገፊ ምክንያት በሐገር…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ። አየር መንገዱ ወደ ሻንግሀይ ከተማ የካቲት 1973 የመጀመሪያ የቻይና በረራውን በማድረግ አገልግሎቱን የጀመረ ሲሆን ከጥቅምት 1973 ጀምሮ ደግሞ መዳረሻውን ወደ ቤጂንግ ከተማ በመቀየር አገልግሎን ቀጥሏል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት በ5 የመንገደኛ እና 9 የእቃ ጭነት መደበኛ በረራዎች በአጠቃላይ 66 ሳምንታዊ በረራዎችን ወደ 10 የቻይና ከተሞች በማድረግ ላይ ይገናል። ቤጂንግ፣ ጓንዡ፣ ሼንጁ፣ሻንግሀይ፣ ሸንዘን ፣ ውሀን፣ቻንግሻ፣ዢያመን፣ቸንዱ እና ሆንግ ኮንግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚበርባቸው የቻይና ከተሞች ናቸው። የአፍሪካ ግዙፍ የአቪዬሽን ተቋም የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች አሉት። በ1945 የተመሰረተው የኢትዮጵያ አየር መንገድ 70ኛ የምስረታ በዓሉን ከአንድ ዓመት በፊት…
Read More
የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና መኮንኖች ኢትዮጵያን ጎበኙ

የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና መኮንኖች ኢትዮጵያን ጎበኙ

የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት የጦር ጀነራሎች እና ከፍተኛ የጦር አመራር መኮንኖች በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገዋል። ኤርትራ ወታደራዊ ልኡክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት፣ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዓቅም እና እየተከናወኑ ያሉ የምርምር እና ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና፤ ኢንስቲትዩቱ እያከናወናቸው ባሉ የቴክኖሎጂ ሥራዎች ዙሪያ ለቡድኑ አባላት ገለጻ ማድረጋቸውን ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል፡፡ የኤርትራ የጦር ጀነራሎች እና ከፍተኛ የጦሩ አመራሮች ቡድን አስተባባሪ ጀነራል አብርሃ ካሳ፤ በኢንስቲትዩቱ ያደረጉት ጉብኝት ለአገራቸው ብዙ ልምድ የቀሰሙበት መሆኑን መናገራቸው ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በቴክኖሎጂው ዘርፍም አብረው መስራት የሚያስችላቸው እድል ስለመኖሩም የተገነዘቡበት ጉብኝት መሆኑን መጠቆማቸውም ተመላክቷል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ከ20 ዓመት በፊት ወደ ደም አፋሳሽ…
Read More
መልቲቾይዝ ኢትዮጵያ ለአማርኛ እና ኦሮሚኛ ተመልካቾች አዳዲስ ፕሮግራሞችን እንደሚያቀርብ አስታወቀ

መልቲቾይዝ ኢትዮጵያ ለአማርኛ እና ኦሮሚኛ ተመልካቾች አዳዲስ ፕሮግራሞችን እንደሚያቀርብ አስታወቀ

ከመልቲቾይዝ ኩባንያዎች መካከል አንዱ የሆነው ዲኤስቲቪ ለኢትዮጵያ ተመልካቾች የተለያዩ መዝናኛ ፕሮግራሞችን በማቅረብ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ድርጅቱ በኢትዮጵያ የይዘት ቀንን በአዲስ አበባ ያከበረ ሲሆን በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ አንጋፋ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ብዙሃን መገኛኛ ባለሙያዎች እና ሌሎችም ተገኝተዋል፡፡ ድርጅቱ በዚህ ወቅት እንዳለው ከዚህ በፊት ለኢትዮጵያ ተመልካቾች ሲያቀርባቸው ከነበሩት የመዝናኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪ አዳዲስ ይዘቶችን እንደሚያቀርብ ገልጿል፡፡ በድርጅቱ በኩል ለኢትዮጵያ ተመልካቾች ይቀርቡ ከነበሩት ይዘቶች በተጨማሪ አዳዲስ ፕሮግራሞችን በአማርኛ እና በኦሮሚኛ ቋንቋዎች የሚተላለፉ ይዘቶችን በቅርቡ እጀምራለሁም ብሏል፡፡ ዲኤስቲቪ አሁን ላይ በአቦል ቲቪ እና አቦል ዱካ ፕሮግራሙ አደይ፣ ደራሽ፣ አስኳላ፣ ሶረኔ፣ አጋሮቹ፣ ገብርዬ እና ሌሎችንም መዝናኛዎች በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ የመልቲቾይዝ ኢትዮጵያ ዳይሬክተር ገሊላ ገብረሚካኤል በፕሮግራሙ ላይ…
Read More
የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የድጎማ በጀት እንደሚልክ ገለጸ

የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የድጎማ በጀት እንደሚልክ ገለጸ

የፌደራል መንግስት ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ለትግራይ ክልል የበጀት ድጎማ መልቀቅ እንደሚጀምር የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ተናግረዋል። ለክልሉ የሚለቀቀው በጀት፤ ለሌሎች ክልሎች እንደሚደረገው ሁሉ በወራት ተከፋፍሎ የሚላክ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። የፌደራል መንግስት ለትግራይ በጀት ለማስተላለፍ ከስምምነት ላይ መድረሱን በተመለከተ አቶ ጌታቸው ረዳ ከቀናት በፊት ተናግረው ነበር። ባለፈው ሳምንት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተሾሙት አቶ ጌታቸው፤ የፌደራል መንግስት በጀት መፍቀዱን፤ ሆኖም የገንዘብ መጠኑን በተመለከተ ግን “ገና እንነጋገራለን” ማለታቸው ይታወሳል። የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታው በበኩላቸው፤ የትግራይ ክልል በጀት “የሚታወቅ” መሆኑን ገልጸዋል። የፌደራል መንግስት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እስኪቋቋም የበጀት ድጎማ ሳይለቅቅ ቢቆይም፤ በክልሉ ውስጥ…
Read More
የኬንያው ኬሲቢ ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ድርሻ ለመግዛት መወሰኑን አስታወቀ

የኬንያው ኬሲቢ ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ድርሻ ለመግዛት መወሰኑን አስታወቀ

ዋና መቀመጫውን ኬንያ ናይሮቢ ያደረገው ኬሲቢ ግሩፕ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ባንኮች የአክሲዮን ድርሻ በመግዛት ወደ ገበያው ለመግባት አማራጮችን እየገመገመ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ ግዙፍ ባንክ የሆነው ኬሲቢ ኬንያን ጨምሮ በቡሩንዲ፣ ሩዋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ታንዛንያ እና ዲሞክራቲክ ኮንጎ በባንክ ኢንዱስትሪ እየሰራ ይገኛል። ይህ ባንክ አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ ባንኮች የአክሲዮን ድርሻ ለመግዛት መወሰኑ ተሰምቷል። ይሁንና የኬንያው ባንክ ከየትኛው የኢትዮጵያ ባንክ አክስዮን ለመግዛት እንደወሰነ አልታወቀም። የባንኩ ፋይናንስ ዳይሬክተር የሆኑት ላውረንስ ኪማቲ ከቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ ጋር በነበራቸው ቆይታ በኢትዮጵያ ባንክ ገበያ ላይ ቅኝተ ማድረጋቸውን ገልጸው፤ ከተለያዩ ባንኮች ሰዎች ጋር መወያየታቸውንም ጠቁመዋል፡፡ ዳይሬክተሩ ከእነርሱ ጋር ሊሠሩ የሚችሉትን መለየታቸውንም በቆይታቸው ተናግረዋል፡፡ እንደ ላውረንስ የባንኮቹ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም የተሻለ…
Read More
አቶ ሮባ መገርሳ ከሀላፊነት ተነሱ

አቶ ሮባ መገርሳ ከሀላፊነት ተነሱ

የኢትዮጵያ ባህር ሎጅስቲክስ አገልግሎትን ላለፉት አምስት ዓመታት በሀላፊነት የመሩት አቶ ሮባ መገርሳ ከሀላፊነት ተነስተዋል። በዚህ ተቋም ከባለሙያነት ጀምሮ ያገለገሉት አቶ ሮባ ለምን ከሀላፊነት እንደተነሱ ይፋ አልተደረገም። በአቶ ሮባ ቦታም በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) ከትናንት መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ መሾማቸውን ኢትዮ ነጋሪ ከተቋሙ የኮሙንኬሽን ሀላፊ አቶ ደምሰው በንቲ አረጋግጣለች። አዲሱ ሀላፊ ከዚህ በፊት በኦሮሚያ ክልል ከወረዳ እስከ ፌደራል ተቋማት በተለያዩ የሀላፊነት ቦታዎች ላይ መስራታቸው ተገልጿል።
Read More
ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ እና ጫት ንግድ ፈተና እንደሆነባት ገለጸች

ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ እና ጫት ንግድ ፈተና እንደሆነባት ገለጸች

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ የሀገሪቱን የውጪ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ እየጎዳው ነው ብለዋል። በዘንድሮው ዓመት የወርቅ እና የጫት ምርት በኮንትሮባንድ ንግድ አማካይነት እየወጣ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት ከአሶሳ 20 ኩንታል ወርቅ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ይላክ ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ በዚህ  ዓመት ግን ሶስት ኩንታል ብቻ መላኩ ለወርቅ ኮንትሮባንድ ንግድ መስፋፋት ማሳያ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ ከእዚህ ባለፈ የታንታለም ምርት በከፍተኛ ደረጃ ጉጂ ላይ ቢመረትም በህጋዊ መንገድ ወደ ውጪ ተልኮ የውጪ ገቢ ከሚያስገኘው ይልቅ በህገ ወጥ መንገድ ለጎረቤት ሀገራት የሚሸጠው ከፍተኛ ቁጥር እንዳለው አክለው አንስተዋል፡፡ ይህንኑ ከፍተኛ…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር ሱፐር አፕ የተሰኘ አገልግሎት መስጫውን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር ሱፐር አፕ የተሰኘ አገልግሎት መስጫውን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም ከዚህ በፊት የተለያዩ አገልግሎቶችን ይሰጥበት የነበረውን "ቴሌ ብር" መተግበሪያ አዘምኗል። ዛሬ ይፋ ያደረገው ይህ የደንበኞች አገልግሎት ከዚህ በፊት በአገልግሎት ላይ ከነበሩት ሶስት ተጨማሪ አገልግሎቶችን መስጠት ያስችላል። አዲሶቹ አገልግሎቶች የታቀደ ክፍያ፣ ለቡድን ገንዘብ መላክ እና የእድል ጨዋታዎችን ማከናወን የሚያስችሉ ናቸው። የታቀደ ክፍያ አገልግሎት ደንበኞች የገንዘብ እና አየር ሰዓት ለመላክ እንዲሁም ወርሀዊ የአገልግሎት ክፍያዎችን በቀኑ ለመክፈል ቀድመው ማቀድ የሚያስችል እንደሆነ ተቋሙ አስታውቋል። ሁለተኛው እና ዛሬ ይፋ የተደረገው የቴሌ ብር ተጨማሪ አገልግሎት ከአንድ በላይ ለሆኑ ተቀባዮች አስቀድመው በሚሞሉት መስፈርት መሰረት በአንዴ መላክ ያስችላልም ተብሏል። ሶስተኛው አዲስ አገልግሎት ደግሞ የእድል ጨዋታ የሚባል ሲሆን አጠቃቀምን መሰረት ያደረገ የአጓጊ ሽልማቶች ባለቤት የሚያደርግ እንደሆነ በፕሮግራሙ…
Read More