stayeasyhotel

በኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ስራዎችን የሰሩ ሰዎች ተሸለሙ

በኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ስራዎችን የሰሩ ሰዎች ተሸለሙ

በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በርካታ የበጎ አድራጎት ስራ የሰሩ ሰዎችን ማመስገን እና ለስራቸው እውቅና መስጠት አላማው ያደረገ ፕሮግራም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ማስተር አብነት ፣ ወንድም ካሊድ ፣ሚኪያስ ለገሰ እና ዘካሪያስ ኪሮስ በኢትዮጵያ ዘር፣ ቀለም እና ሀይማኖት ሳይገድባቸው የተቸገሩ ወገኖችን ለዓመታት እየረዱ መሆናቸው በመድረኩ ላይ ተጠቅሷል። ግለሰቦቹ ለሰሩት በጎ ስራ በሽማግሌዎች ምርቃት ታጅበው የምስጋና እና የእውቅና መርሀግብር ተካሂዷል። በአዲስ አበባ ስቴይ ኢዚ ሆቴል በተካሄደው በዚህ ፕሮግራም ላይ የመንግስት አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል። ምስጋና እና እውቅና ከተሰጣቸው ሰዎች መካከልም በአዲስ አበባ በበጎ ስራቸው  የተቸገሩ ሰዎች እንዲረዱ እና ህክምና  እንዲያገኙ በማድረግ የሚታወቁት ሚኪያስ ለገሰ ( የሰሊሆም የአዕምሮ መርጃ ማዕከል)…
Read More
በአዲስ አበባ በ1 ነጥብ 5 ቢልየን ብር ወጪ የተገነባው “ስቴይ ኢዚ ፕላስ” ሆቴል ወደ ሥራ ሊገባ ነው

በአዲስ አበባ በ1 ነጥብ 5 ቢልየን ብር ወጪ የተገነባው “ስቴይ ኢዚ ፕላስ” ሆቴል ወደ ሥራ ሊገባ ነው

በአዲስ አበባ ከአዲሱ ገበያ ከፍ ብሎ እንጦጦ መስመር ላይ የተገነባው፤ "ስቴይ ኢዚ ፕላስ" ሆቴል ከኹለት ሳምንታት በኋላ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ የሆቴሉ ስራ አስኪያጅ አቶ አሚር ሰኢድ እንዳሉት ሆቴሉ በጥንዶቹ ዳግማዊ መኮንን እና ህይወት አየለ ባለቤትነት የተገነባ ሲሆን ሆቴሉ ከአንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ ፈጅቷል ብለዋል፡፡ በአምስት ዓመት ውስጥ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ታስቦ ግንባታው የተጀመረው ይህ ባለ ስምንት ወለል ህንጻ ኮሮና ቫይራ ተጨምሮበት በስምንት ዓመት ውስጥ መጠናቀቁን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ሆቴሉ በባለ አምሰት ኮከብ ደረጃ መገንባቱን የተናገሩት ደግሞ የሆቴሉ ባለቤት እና ማኔጂንግ ዳይሬክተር ወይዘሮ ሂወት አየለ ናቸው፡፡ እንደ ወይዘሮ ሂወት ገለጻ ሆቴሉ በአጠቃላይ 103 ክፍሎች፣ ከ15 እስከ 1 ሺሕ…
Read More