Humanity

በኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ስራዎችን የሰሩ ሰዎች ተሸለሙ

በኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ስራዎችን የሰሩ ሰዎች ተሸለሙ

በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በርካታ የበጎ አድራጎት ስራ የሰሩ ሰዎችን ማመስገን እና ለስራቸው እውቅና መስጠት አላማው ያደረገ ፕሮግራም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ማስተር አብነት ፣ ወንድም ካሊድ ፣ሚኪያስ ለገሰ እና ዘካሪያስ ኪሮስ በኢትዮጵያ ዘር፣ ቀለም እና ሀይማኖት ሳይገድባቸው የተቸገሩ ወገኖችን ለዓመታት እየረዱ መሆናቸው በመድረኩ ላይ ተጠቅሷል። ግለሰቦቹ ለሰሩት በጎ ስራ በሽማግሌዎች ምርቃት ታጅበው የምስጋና እና የእውቅና መርሀግብር ተካሂዷል። በአዲስ አበባ ስቴይ ኢዚ ሆቴል በተካሄደው በዚህ ፕሮግራም ላይ የመንግስት አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል። ምስጋና እና እውቅና ከተሰጣቸው ሰዎች መካከልም በአዲስ አበባ በበጎ ስራቸው  የተቸገሩ ሰዎች እንዲረዱ እና ህክምና  እንዲያገኙ በማድረግ የሚታወቁት ሚኪያስ ለገሰ ( የሰሊሆም የአዕምሮ መርጃ ማዕከል)…
Read More