Mediaethiopia

የኢትዮጵያ ሚዲያዎች በጥቃት ውስጥ እንደሚገኙ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሚዲያዎች በጥቃት ውስጥ እንደሚገኙ ተገለጸ

ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ብቻ 29 ጋዜጠኞች በታሰሩባት ኢትዮጵያ፤ የፕሬስ ነጻነት “ጉልህ ጥቃት” እንዳጋጠመው ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና የደቡባዊ አፍሪካ ሚዲያ ኢንስቲትዩት አስታወቁ። ባለስልጣናት የፕሬስ ነጻነትን ማፈን በሚፈልጉባቸው በምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ሀገራት፤ በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰው ጥቃት እየጨመረ መምጣቱንም ተቋማቱ ገልጸዋል። ሁለቱ ተቋማት ይህን ያሉት ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 25፤ 2015 ታስቦ የሚውለውን የዓለም የፕሬስ ነጻነትን በማስመልከት በጋራ ባወጡት ዳሰሳ ነው። ዳሰሳው ኢትዮጵያን ጨምሮ በ10 የአፍሪካ ሀገራት ያለውን የመገናኛ ብዙሃን ነጻነትን እና በጋዜጠኞች ላይ እየደረሱ ያሉ ጥቃቶችን በማሳያነት በማንሳት ዳሰሳ አድርጓል። በዚሁ ዳሰሳ፤ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት በርካታ ጋዜጠኞችን በማሰር ከኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በመለጠቅ ስሟ የተጠቀሰው ኢትዮጵያ ነች።…
Read More
በኢትዮጵያ ተጨማሪ አምስት ቴሌቪዥኖች ወደ ስርጭት ሊገቡ ነው ተባለ

በኢትዮጵያ ተጨማሪ አምስት ቴሌቪዥኖች ወደ ስርጭት ሊገቡ ነው ተባለ

አምስት የንግድ የቴሊቪዥን ጣቢያዎች የስርጭት ፈቃድ ሊሰጣቸው እንደሆነ ተገልጿል፡፡ አምስት የንግድ የሳተላይት ቴሌቪዥን ብሮድካስት አገልግሎት ጣቢያዎች ፈቃድ እንዲሰጣቸው  መወሰኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን አስታውቋል። ፈቃዱን የሚያገኙት ጎህ ቴሌቪዥን፣ ኤፕላስ ቲቪ፣ ሸካል ቲቪ፣ ከገበሬው ቴሌቪዥን እና ኢሲኤን ቴሌቪዥን መሆናቸውን ባለስልጣኑ አስታውቋል። ፈቃድ የሚሰጣቸውም የገንዘብ አቅምና ምንጫቸው ስራውን ለማስኬድ አስተማማኝ እንደሆነ በመታመኑ ነው ያለው ባለስልጣኑ፣ አገልግሎቱን ለመስጠት ድርጅታዊ ብቃት ያላቸው መሆኑ መጣራቱ ተገልጿል፡፡ እንዲሁም የፕሮጀክት ሰነዳቸው፣ ያቀረቧቸው መሳሪያዎችና ቴክኖሎጂዎች አገልግሎቱን ለመስጠት ብቃት ያላቸው መሆናቸው ተጣርቶ መወሰኑን ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡ የንግድ ቴሌቪዥን ፈቃድ ለማገኘት የቀረቡ አመልካቾች በባለሥልጣኑ መስሪያ ቤት በመቅረብ ውል እንዲዋዋሉና ከዛሬ ጅምሮ ፈቃዳቸውን መውሰድ እንደሚችሉም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።…
Read More