Pressfreedom

አዲሱ የኢትዮጵያ ሚዲያ ህግ ማሻሻያ ከሚዲያ እና ህግ ባለሙያዎች ማህበራት ተቃውሞ ገጠመው

አዲሱ የኢትዮጵያ ሚዲያ ህግ ማሻሻያ ከሚዲያ እና ህግ ባለሙያዎች ማህበራት ተቃውሞ ገጠመው

የሚዲያ ህግ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ሁሉን ያሳተፈ ውይይት በአስቸኳይ እንዲደረግበት  ተጠይቋል፡፡ ከአንድ ወር በፊት በስራ ላይ ያለው የሚዲያ ህግ እንዲሻሻል ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡ ይታወሳል፡፡ ይህ ረቂቅ አዋጅ በቂ የባለድርሻ አካላት ውይይት ሳይደረግበት ወደ ቋሚ ኮሚቴ መመራቱ ትክክል እንዳልሆነ በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የጋዜጠኞች፣ ህግ እና ሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ማህበራት ተችተዋል፡፡ 14 የጋዜጠኞች፣ ህግ እና ሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ማህበራት በጋራ ባወጡት መግለጫ የሚዲያ ህግ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የሕዝብንም ሆነ የባለድርሻ አካላትን ድምፅ በተገቢ ያላካተተ ነው ሲሉ ተችተዋል፡፡ የጋዜጠኞች ማህበራት እና የሰብዓዊ መብት ድርጅቶቹ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሁለት ሳምንት በፊት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013ን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ…
Read More
ኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት የማይከበርባት ሀገር ናት መባሏን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት የማይከበርባት ሀገር ናት መባሏን ውድቅ አደረገች

የኢትዮጵያ መንግስት ምዕራባውያን በፕሬስ ነጻነት አያያዝ ዙሪያ ያቀረቡበትን ትችት እንደማይቀበለው አስታውቋል፡፡ ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ 18 ምዕራባውያን ሀገራት ኢምቢሲዎች 'የዓለም የፕሬስ ነጻነት ቀንን' አስመልክተው ባወጡት የጋራ መግለጫ የኢትዮጵያን የጋዜጠኞች አያያዝ ተችተዋል። በኢትዮጵያ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እንዲከበር ከጠየቁ ሀገራት መካከልም አሜሪካ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ብሪታንያ፣ ጀርመን፣ ስዊድን፣ ቤልጂየም፣ ኖርዌይ፣ ስፔን፣ ኔዘርላንድ እና ሌሎችም ይገኛሉ፡፡ ሀገራቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ጋዜጠኞች ስራቸውን በመስራታቸው "ማስፈራሪያ እና እስር ይደርሰባቸዋል" ብለዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይህን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ ሀገራቱ በኢምባሲዎቻቸው በኩል ያወጡትን መግለጫ እንደማይቀበለው ገልጿል። ኢትዮጵያ ከሁሉም አጋሮቿ እና ባለድርሻ አካላት ጋር ገንቢ የሆነ ንግግር ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን የገለጸው ሚኒስቴሩ "አባታዊ ወደሆነ መግለጫ ማምራት የሁለትዮሽ ግንኙነት…
Read More
የኢትዮጵያ ሚዲያዎች በጥቃት ውስጥ እንደሚገኙ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሚዲያዎች በጥቃት ውስጥ እንደሚገኙ ተገለጸ

ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ብቻ 29 ጋዜጠኞች በታሰሩባት ኢትዮጵያ፤ የፕሬስ ነጻነት “ጉልህ ጥቃት” እንዳጋጠመው ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና የደቡባዊ አፍሪካ ሚዲያ ኢንስቲትዩት አስታወቁ። ባለስልጣናት የፕሬስ ነጻነትን ማፈን በሚፈልጉባቸው በምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ሀገራት፤ በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰው ጥቃት እየጨመረ መምጣቱንም ተቋማቱ ገልጸዋል። ሁለቱ ተቋማት ይህን ያሉት ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 25፤ 2015 ታስቦ የሚውለውን የዓለም የፕሬስ ነጻነትን በማስመልከት በጋራ ባወጡት ዳሰሳ ነው። ዳሰሳው ኢትዮጵያን ጨምሮ በ10 የአፍሪካ ሀገራት ያለውን የመገናኛ ብዙሃን ነጻነትን እና በጋዜጠኞች ላይ እየደረሱ ያሉ ጥቃቶችን በማሳያነት በማንሳት ዳሰሳ አድርጓል። በዚሁ ዳሰሳ፤ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት በርካታ ጋዜጠኞችን በማሰር ከኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በመለጠቅ ስሟ የተጠቀሰው ኢትዮጵያ ነች።…
Read More