Journalism

ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን ከሚያስሩ ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ተካተተች

ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን ከሚያስሩ ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ተካተተች

በመላው አፍሪካ 67 ጋዜጠኞች በስራቸው ምክንያት ብቻ መታሰራቸውን አለም አቀፉ የጋዜጠኞች ጥበቃ ኮሚቴ (ሲፒጄ) ሪፖርት ያስረዳል። የተመዘገበው እስር በአፍሪካ በነጻ ሀሳብን የመግለጽ መብት ፣ የመረጃ ነጻነት እና ሌሎችም መብቶች እያሽቆለቆሉ እንደሚገኙ ማሳያ ነው ብሏል ሪፖርቱ ፡፡ ለጋዜጠኞች መብት የሚሟገተው ሲፒጄ እስከ ታህሳስ 1 ቀን ድረስ በአለም አቀፍ ደረጃ 361 ጋዜጠኞች መታሰራቸውን የገለጸ ሲሆን በአፍሪካ የተመዘገበው ዕስር እስከዛሬ ከነበሩት በመጠኑ ሁለተኛው ነው ተብሏል። በሲፒጄ የአፍሪካ ፕሮግራም አስተባባሪ ሙቶኪ ሙሞ “መንግስታት በጋዜጠኞች ላይ የብሔራዊ ደህንነት፣ የፀረ-ሽብርተኝነት እና የሳይበር ወንጀል ህጎችን በመሳሪያነት በመጠቀም ጋዜጠኞችን ለማሳደድ እና ለማሰር እያዋሉት እንደሚገኙ” ተናግረዋል፡፡ አስተባባሪው እነዚህ አዝማሚያዎች በአፍሪካ ብቻ የተገደቡ ባይሆኑም በአህጉሪቱ በእንደዚህ አይነት ህጎች ክስ የሚመሰረትባቸው…
Read More
የትግራይ ቲቪ ጋዜጠኞቹ ታገቱ

የትግራይ ቲቪ ጋዜጠኞቹ ታገቱ

ሚዲያው እንደገለጸው ከህገወጥ የወርቅ ማውጣት ሂደት ጋር በተያያዘ መረጃ በማሰባሰብ ላይ የነበሩ ጋዜጤኞቹ  በታጣቂዎች ታግተው ተወስደዋል። በትግራይ ክልል ሰሜን ምዕራብ ዞን ያለውን ህገወጥ የወርቅ ማዕድን የማውጣት ሂደትና የጎንዮሽ ጉዳቶቹ እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ዘገባ ለመስራት ወደ ስፍራው ያቀናው የጋዜጠኞች ቡድን በታጣቂዎች ታግተዋል ሲል ተገልጿል። ሶስት ባለሙያዎችን የያዘው የጋዜጠኞች ቡድኑ ታህሳስ 20 ቀን 2017 ዓ/ም ጥዋት 3 ሰዓት በአስገደ ወረዳ፣ መይሊ ከተባለው ስፍራ ወጣ ብሎ በሚገኘውን መንደር በታጣቂዎች ተይዘዋል ተብሏል። ጋዜጠኞቹ ላለፉት ሶስት ቀናት በቦታው ተገኝተው ስላለው ነገር ከአካባቢው ነዋሪዎች መረጃዎችን ሲያሰባስቡ የቆዩ ሲሆን በተለይም በመይሊ አካባቢ ማዕድናቱን ለማውጣት በጥቅም ላይ እየዋሉ የሚገኙ የተለያዩ ጎጂ ኬሚካሎች እያደረሱት ያለውን ጉዳት በተመለከተ መረጃዎች…
Read More
አዲሱ የኢትዮጵያ ሚዲያ ህግ ማሻሻያ ከሚዲያ እና ህግ ባለሙያዎች ማህበራት ተቃውሞ ገጠመው

አዲሱ የኢትዮጵያ ሚዲያ ህግ ማሻሻያ ከሚዲያ እና ህግ ባለሙያዎች ማህበራት ተቃውሞ ገጠመው

የሚዲያ ህግ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ሁሉን ያሳተፈ ውይይት በአስቸኳይ እንዲደረግበት  ተጠይቋል፡፡ ከአንድ ወር በፊት በስራ ላይ ያለው የሚዲያ ህግ እንዲሻሻል ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡ ይታወሳል፡፡ ይህ ረቂቅ አዋጅ በቂ የባለድርሻ አካላት ውይይት ሳይደረግበት ወደ ቋሚ ኮሚቴ መመራቱ ትክክል እንዳልሆነ በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የጋዜጠኞች፣ ህግ እና ሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ማህበራት ተችተዋል፡፡ 14 የጋዜጠኞች፣ ህግ እና ሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ማህበራት በጋራ ባወጡት መግለጫ የሚዲያ ህግ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የሕዝብንም ሆነ የባለድርሻ አካላትን ድምፅ በተገቢ ያላካተተ ነው ሲሉ ተችተዋል፡፡ የጋዜጠኞች ማህበራት እና የሰብዓዊ መብት ድርጅቶቹ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሁለት ሳምንት በፊት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013ን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ…
Read More
በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች ፍትህ እንዲያገኙ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበር ጥሪ አቀረበ

በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች ፍትህ እንዲያገኙ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበር ጥሪ አቀረበ

መንግስት በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች ፍትህ እንዲያገኙ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበር ጠይቋል። ማህበሩ የጋዜጠኞቹ የፍርድ ሂደትም ከፖለቲካ አተያይ በፀዳ መንገድ እንዲሆን ጥሪውን ያቀርባል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማኅበር አዲስ ሥራ አስፈጻሚ አባላት በአዲ አበባ ቃሊቲና ቂሊንጦ ማረሚያ ቤቶች በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞችን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝታቸውም ስለ ማረሚያ ቤት አያያዝ እና አጠቃላይ የፍትህ ሂደቱ ያለበትን ሁኔታ ከጋዜጠኞቹ ጋር እንደተወያዩ ማህበሩ በመግለጫው ላይ ጠቅሷል፡፡ ጋዜጠኞቹ በማረሚያ ቤቶቹ አያያዝ በኩል ቅሬታ ባይኖራቸውም በፖሊስ ቁጥጥር ስር በተያዙበት ወቅት የተያዙበት መንገድም ሆነ ከተያዙ በኃላ ያለው የፍርድ ቤት ሂደት አግባብነት እንደሚጎድለው ተናግረዋል፡፡ በሁለቱም ማረሚያ ቤቶች ከአንድ ዓመት በላይ ሳይፈረድባቸው የታሰሩ ጋዜጠኞች መኖራቸውን ማኅበሩ እንዳረጋገጠ አስታውቋል። ስለሆነም…
Read More
ጋዜጠኛ ሳሙኤል አሰፋ ከአገር ለመሰደድ መገደዱን ተናገረ

ጋዜጠኛ ሳሙኤል አሰፋ ከአገር ለመሰደድ መገደዱን ተናገረ

ጋዜጠኛ ሳሙኤል አሰፋ በዋዜማ ሬዲዮ፣ ኢኤምኤስ እና ሌሎችም ሚዲያዎች በጋዜጠኝነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡ ከወራት በፊት በአዲስ አበባ ዙሪያ ሸገር ከተማ "ሕገ ወጥ ግንባታ" ናቸው ተብለው በፈረሱ ወደ 100 ሺህ የሚቆጠሩ መኖሪያ ቤቶችና በተፈናቀሉ ዜጎች ጉዳይ ለዘገባ ወደ ስፍራው ባመራበት ወቅት በፖሊስ ተይዞ ለእስር ተዳርጎም ነበር፡፡ በዚህ ወቅት በፖሊስ ድብደባ፣ እስርና ማዋከብ ደርሶበት እንደነበር የተናገረው ጋዜጠኛ ሳሙኤል አሰፋ በዋስ ከእስር ቤት ወጥቶ እንዲከራከር በፍርድ ቤት ተወስኖለት ቢወጣም ዛቻና ማስፈራሪ ሲደርስበት እንደነበረ ለኢትዮ ነጋሪ ተናግሯል፡፡ በቅርቡም ለዋዜማ ሬድዮ እና ኢንተር ኒውስ ዘገባ ለመስራት ወደ አማራ ክልል ደሴና ሐይቅ ከተሞች በተጓዘበት ወቅት በክልሉ ኮማንድ ፖስት ታስሮ እንደነበረም አክሏል። አስቀድሞ በታሰረበት ጉዳይ ለዋስትና የተያዘውን ገንዘብ…
Read More
ኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት የማይከበርባት ሀገር ናት መባሏን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት የማይከበርባት ሀገር ናት መባሏን ውድቅ አደረገች

የኢትዮጵያ መንግስት ምዕራባውያን በፕሬስ ነጻነት አያያዝ ዙሪያ ያቀረቡበትን ትችት እንደማይቀበለው አስታውቋል፡፡ ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ 18 ምዕራባውያን ሀገራት ኢምቢሲዎች 'የዓለም የፕሬስ ነጻነት ቀንን' አስመልክተው ባወጡት የጋራ መግለጫ የኢትዮጵያን የጋዜጠኞች አያያዝ ተችተዋል። በኢትዮጵያ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እንዲከበር ከጠየቁ ሀገራት መካከልም አሜሪካ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ብሪታንያ፣ ጀርመን፣ ስዊድን፣ ቤልጂየም፣ ኖርዌይ፣ ስፔን፣ ኔዘርላንድ እና ሌሎችም ይገኛሉ፡፡ ሀገራቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ጋዜጠኞች ስራቸውን በመስራታቸው "ማስፈራሪያ እና እስር ይደርሰባቸዋል" ብለዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይህን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ ሀገራቱ በኢምባሲዎቻቸው በኩል ያወጡትን መግለጫ እንደማይቀበለው ገልጿል። ኢትዮጵያ ከሁሉም አጋሮቿ እና ባለድርሻ አካላት ጋር ገንቢ የሆነ ንግግር ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን የገለጸው ሚኒስቴሩ "አባታዊ ወደሆነ መግለጫ ማምራት የሁለትዮሽ ግንኙነት…
Read More
መንግሥት ጋዜጠኛ በላይ ማናዬን ከእስር እንዲለቅ ሲፒጂ ጠየቀ

መንግሥት ጋዜጠኛ በላይ ማናዬን ከእስር እንዲለቅ ሲፒጂ ጠየቀ

የኢትዮ ኒውስ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም የጸጥታ ክልሎች አራት ኪሎ በሚገኘው ከቢሮው አካባቢ እንዳሰሩት የስራ ባልደረባው እና ባለቤቱ ተናግረዋል። የጋዜጠኞች መሽት ተሟጋች የሆነው ሲፒጂ ባወጣው ሪፖርት ጋዜጠኛ በላይ ከታሰረ ሶስት ሳምንት እንዳለፈው እና እስካሁን ፍርድ ቤትም እንዳልቀረበ አስታውቋል። የሲፒጂ ሰብሰሀራ አፍሪካ ተወካይ የሆኑት ሙቶኪ ሙሞ እንዳሉት በኢትዮጵያ ጋዜጠኞች የመስራት ነጻነታቸው መጎዳቱን ተናግረዋል ። የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋዜጠኛ በላይ ማናዬን በአስቸኳይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከእስር እንዲለቅ ሲፒጂ አሳስቧል። እንዲሁም የኢትዮጵያ መንግሥት የጋዜጠኞችን እስር እንዲያቆምም ሲፒጂ ጥሪ አቅርቧል። የጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ባለቤት በላይነሽ ንጋቱ ባለቤቷ አንድ ጊዜ ከታሰረበት ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ሄዳ እንደጠየቀችው የተናገረች ሲሆን በአማራ ክልል…
Read More
ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን መታሰሩ ተገለጸ

ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን መታሰሩ ተገለጸ

የትርታ ኤፍ  ኤም መስራች ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን በፌደራል ፖሊሶች ተይዞ መወሰዱን ባለቤቱ ገልፃለች። ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን ዛሬ ምሳ ሰዓት ላይ ባልዳራስ ኮንዶሚኒየም ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በፌደራል ፖሊስ አባላት ተይዞ  ሜክሲኮ የቀድሞው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ወደሚገኘው ጊዜያዊ ማቆያ ቦታ መወሰዱን ባለቤቷ ገልፃለች ። ባለቤቱ የታሰረበት ቦታ ሄዳ የጠየቀች ሲሆን በምን ምክንያት እንደታሰረ እንዳላወቀና ለጥያቄም እንዳልቀረበ አሳውቋታል ። ጋዜጠኛ የኋላሸት ትኩረቱን በኪነ ጥበባዊ ጉዳዮች ላይ ያደረገው ኪነ ብስራት የተሰኘ የሬድዮ ሾው ለዓመታት በብስራት ኤፍ ኤም 101.1 በማቅረብ ይታወቃል። ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ጥበቃ ቡድን ወይም ሲፒጂ ከቀናት በፊት ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ የጋዜጠኞች እስር መቀጠሉን እና የታሰሩት እንዲፈቱ ማሳሰቡ ይታወሳል።
Read More
በሽብር ወንጀል የተከሰሱ ጋዜጠኞች የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቆ ሆኖ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ተወሰነ

በሽብር ወንጀል የተከሰሱ ጋዜጠኞች የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቆ ሆኖ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ተወሰነ

አራት የመገናኛ ብዙሃን ጋዜጠኞች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ በፍርድ ቤት ውድቅ ተደረጓል። በሽብር ወንጀል የተከሰሱ አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ፤ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውድቅ ተደረገ። የተከሳሾችን በቁጥጥር ስር መዋል በተመለከተ የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ያወጣውን መግለጫ በድረ ገጻቸው የጫኑ መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎቻቸውን እንዲያወርዱም ፍርድ ቤቱ አዝዟል። ይህን ትዕዛዝ የሰጠው ሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም የዋለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ችሎት ነው። ችሎቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጎ ትዕዛዞችን በሰጠበት ቅጽበት ተከሳሾች በጭብጨባ የታጀበ መፈክር አሰምተዋል። የተከሳሾቹ መፈክር እና ጭብጨባ፤ የችሎት ውሎ…
Read More
ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው በአዲስ ወንጀል ተጠርጥረው ታሰሩ

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው በአዲስ ወንጀል ተጠርጥረው ታሰሩ

በ20 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቁ በፍርድ ቤት የተወሰነላቸው ጋዜጠኞች ፌደራል ፖሊስ በሌላ ወንጀል እንደሚጠረጥራቸው አስታውቋል፡፡ ከ15 ቀን በፊት የታሰሩት ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ታዎድሮስ አስፋው በአቶ ግርማ የሺጥላ ግድያና በሽብርተኝነት ተጠርጥረዋል። ጋዜጠኞቹ ከሰሞኑ ፍርድ ቤት ቀርበው በ20 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ የተወሰነላቸው ቢሆንም ፌደራል ፖሊስ በአዲስ ወንጀል እንደሚጠረጥራቸው ለፍርድ ቤት ባቀረበው ማመልከቻ ጠይቋል፡፡ አዲሱ የፌደራል ፖሊስ የፍርድ ቤት ማመልከቻ እንደሚያስረዳው ጋዜጠኞቹ ከሀገር ውስጥ እስከ ውጪ ሀገር የገቢ ማሰባሰቢያ መንገድ በመዘርጋት ዜጎች ለሽብር እና አመጽ እንዲነሳሱ ቀስቅሰዋል ይላል፡፡ በዚህም መሰረት ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ ተጠርጣሪዎቹ ለተጨማሪ 15 ቀናት ታስረው እንዲቆዩ ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡ ከፌደራል ፖሊስ ምርመራ ቢሮ ማመልከቻ የቀረበለት የልደታ…
Read More