ኢኮኖሚ

ኢትዮ ቴሌኮም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 62 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለጸ።

ኢትዮ ቴሌኮም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 62 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለጸ።

ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር የ 43.3 በመቶ ወይም 18.9 ቢሊዮን ብር እድገት አሳይቷል ብሏል። ገቢውም የእቅዱን 90.7 መሆኑን ተናግሯል። በዘንድሮ የበጀት ዓመት ስድስት ወር ውስጥ ምንም አይነት የሳይበር ጥቃት አልደረሰብኝም ነው ያለው። በዚሁ የስራ አፈፃፀም የግዜ ማዕቀፍ 6 ሚሊዮን ገደማ ደንበኞች አፍርቻለሁ ያለው ኩባንያው በአጠቃላይ የደንበኞቼ ቁጥርም 80.5 ሚሊየን ደርሰዋል ተብሏል። ኢትዮ ቴሌኮም በቴሌኮም አገልግሎት ብዛት ከአፍሪካ 1ኛ ከዓለም ደግሞ 17ኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን ዓለም አቀፉ የቴሌኮም አገልግሎት ድርጅት ወይም ጂ.ኤስ.ኤም.ኤ (GSMA) ጥናት ተረጋግጧል ተብሏል። የደንበኛን ቁጥር ለመጨመር ከተሰሩት ስራዎች መካከል በግማሽ አመቱ 202 አዳዲስ የሞባይል ጣቢያዎች ተጠናቀው ወደ እንደገቡም ተገልጿል። በሞባይል ኔትዎርክ በተከናወኑ የፕሮጀክት ስራዎች ተጨማሪ…
Read More
መንግስት በዩኤስኤይድ ጉዳይ የዲፕሎማሲ ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

መንግስት በዩኤስኤይድ ጉዳይ የዲፕሎማሲ ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

መንግስት በዩኤስኤይድ ጉዳይ የዲፕሎማሲ ድጋፍ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ጠየቀ፡፡ ከአንድ ወር በፊት የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው ወደ ስልጣን የመጡት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ የረድኤት ድርጅት ወይም ዩኤስኤይድ ከአስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታዎች ውጪ ሌሎች ስራዎቹን እንዳይሰራ ማገዳቸው ይታወሳል፡፡ ይህን ተከትሎም ከድርጅቱ ድጋፍ ከሚደረግላቸው ሀገራት መካከል አንዷ በሆነችው ኢትዮጵያ ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል፡፡ በኢትዮጵያ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የሲቪክ ማህበራት ድርጅቶች ከዩኤስኤድ ጋር ሲሰሩ እንደነበር እና ውሳኔው ከባድ ተጽዕኖ ሊኖረው እንደሚችል የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት አስታውቋል፡፡ ከ5 ሺህ በላይ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችን በአባልነት የያዘው የዚህ የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ አህመድ ሁሴን ለአል ዐይን እንዳሉት በዩኤስኤይድ ላይ የተላለፈው የ90 ቀናት ውሳኔ ከምንም…
Read More
ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ባትሪ ማምረቻ ኢንዱስትሪ ልታቋቁም መሆኗ ተገለጸ

ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ባትሪ ማምረቻ ኢንዱስትሪ ልታቋቁም መሆኗ ተገለጸ

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸሙን ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ለሚኒስትሩ ከቀረቡላቸው ጥያቄዎች መካከል በኢትዮጵያ  የኤልክትሪክ መኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካዎች ቁጥራቸው እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ የመለዋወጫ አካላት ፍላጎትን እንዴት ሊሸፈን ታስቧል? የሚለው ዋነኛው ነበር፡፡ ከኤሌክትሪክ መኪና ውስጥ የባትሪ ጉዳይ ዋናው በመሆኑ ወደ ፊት ለባትሪ የሚወጣው ውጪ ምንዛሪ ፈታኝ እንዳይሆን በሃገር ውስጥ ለማምረት የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ምን እየሰራ ነው ሲሉም የምክር ቤቱ አባላት ጠይቀዋል፡፡ አቶ መላኩ በምላሻቸው የኤሌክትሪክ መኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካዎች በክልሎችም ጭምር እየጨመረ መምጣቱን መልካም ነው ምክንያቱም ሃገሪቱ በየአመቱ ለነዳጅ የምታወጣውን 4 ቢልዮን ዶላር ያስቀራል ብለዋል፡፡ የኤሌክትሪክ መኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካዎች እየበረከቱ…
Read More
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ  ሠራተኞች  የሥራ ማቆም አድማ ላይ መቱ

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ  ሠራተኞች  የሥራ ማቆም አድማ ላይ መቱ

400 ያህል የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ የጥሪ ማዕከል ሠራተኞች "አይሶን ኤክስፔሪያንስ" የተሰኘ ወኪል ድርጅት ይፈጸምብናል ባሉት የአስተዳደር በደል ሳቢያ ላለፉት 2 ቀናት የሥራ ማቆም አድማ ላይ መሆናቸውን ዋዜማ ዘግቧል። ሠራተኞቹ በዋናነት የሥራ ማቆም አድማ ያደረጉት፤ በወኪል ድርጅቱ በኩል የሚከፈላቸው ደመወዝ ዝቅተኛ በመሆኑ እንደሆነ ታውቋል። ወኪል ድርጅቱ ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋይ ሠራተኞችን በተጠና መልኩ ከሥራ እንዲሰናበቱ እያደረገ እንደሆነና ባለፈው ዓመት መጋቢት ወር ብቻ 80 ያህል ሠራተኞችን ሕጋዊነቱን ባልተከተለ መንገድ እንዳሰናበተ ተነግሯል ። ተመሳሳይ የሥራ ዓይነት ለሚሠሩ ሠራተኞች፣ ቋንቋንና ማንነትን መሠረት ያደረገ ሕገወጥ የደመወዝ ልዩነትና አድሎ እንዳለና ድርጅቱ ችግሩን እንዲያስተካክል በተደጋጋሚ ተጠይቆ ሊያስተካክል እንዳልቻለ የድርጅቱ ሰራተኛ ማኅበር አስታውቋል ። የድርጅቱ እህት ኩባንያ የሆነው ሳፋሪኮም…
Read More
የኢትዮጵያ ውጭ እዳ መጠን ወደ 31 ቢሊዮን ዶላር አሻቀበ

የኢትዮጵያ ውጭ እዳ መጠን ወደ 31 ቢሊዮን ዶላር አሻቀበ

የአገሪቱ የውጭ ዕዳ መጠን በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. ከነበረበት 28.8 ቢሊዮን ዶላር ወደ 31 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ማለቱን የገንዘብ ሚኒስቴር በቅርቡ ባወጣው የሩብ ዓመት አጠቃላይ የመንግሥት የዕዳ ሰነድ አመላክቷል። ለዚህ እንደምክንያት የተጠቀሰዉ ገበያ መር የውጭ ምንዛሪ ግብይት ተግባራዊ መደረጉና በተጠቀሱት ሦስት ወራት ውስጥ መንግሥት ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ድርጅት (IMF) እና ዓለም ባንክ በድምሩ 1.6 ቢሊዮን ዶላር ብድር የተለቀቀለት በመሆኑ ነዉ ተብሏል። የዕዳ ሰነዱ እንደሚያሳየዉ የውጭ ምንዛሪ ለውጡ ከመደረጉ አንድ ወር በፊት ማለትም በሰኔ 2016 ዓ.ም. የአገሪቱ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት በገንዘብ ሲሰላ 207 ቢሊዮን ዶላር የነበረ ሲሆን በ2017 ዓ.ም. መስከረም ወር መጨረሻ ላይ ወደ 100 ቢሊዮን ዶላር ወርዷል። የአገሪቱ ጂዲፒ…
Read More
ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ቻርጅ ማድረጊያ የሌላቸው ድርጅቶች መኪና ወደ ሀገር ውስጥ እንዳያስገቡ ከለከለች

ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ቻርጅ ማድረጊያ የሌላቸው ድርጅቶች መኪና ወደ ሀገር ውስጥ እንዳያስገቡ ከለከለች

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ነዳጅ ማደያዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያ ለመቀየር ጥናት እየተደረገ  መሆኑን የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወርቁ ደስታ እንዳሉት  "በሁለተኛው ምዕራፍ እየተከናወነ ባለው የአዲስ አበባ ኮሪደር ልማት በመኪና ማቆሚያዎች የኃይል መሙያ እየተሠራ ነው " ብለዋል።የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ዴዔታ በርኦ ሀሰን በበኩላቸው "ከዚህ በኃላ የተሽከርካሪ አስመጪና የሚገጣጥሙ ድርጅቶች የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ የኃይል መሙያ ሳይተክሉ በሥራ ላይ መሰማራት አይችሉም " ብለዋል።በኢትዮጵያ ከ400 በላይ ተቋማት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ እያስመጡና እየገጣጠሙ ነው የተባለ ሲሆን ሁሉም አስመጪዎች እና ገጣጣሚዎች የኃይል መሙያ እንዳላቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከአንድ ሳምንት በፊት  ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል መሙያ ማሽን (ቻርጀር) መትከል የሚፈቅድ መመሪያ ማዘጋጀቷ…
Read More
ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መኪኖች አዲስ መመሪያ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መኪኖች አዲስ መመሪያ አዘጋጀች

ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል መሙያ ማሽን (ቻርጀር) መትከል የሚፈቅድ መመሪያ ጸደቀ መመሪያው በመንገዶች ግራና ቀኝ በየ50 ኪሎሜትር ልዩነት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መሙላት የሚችል ፈጣን ቻርጀር ጣቢያ ማቋቋም ይፈቅዳል፡፡ ይሁንና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል ማቅረብ የሚፈልጉ ተቋማት ከነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ፈቃድ በመውሰድ እንዳለባቸው መመሪያ ይገልጻል። በተለያዩ ተቋማት የሚተከሉ የኤሌክትሪክ ሃይል መሙያዎች ከባለስልጣኑ ፈቃድ ማግኘት እንደሚጠበቅባቸው ይደነግጋል፡፡ ነገር ግን በግል በቤት ውስጥ ከሚተከሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሃይል መሙሊያ ማሽኖች ፈቃድ መጠየቅ የማይጠበቅባቸው መሆኑን ያመላከተው የተቋሙ መረጃ ከዚህ ውጭ ግን ማናቸውም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሃይል ሙሌት የሚሰጡ ማሽኖች መትከል የሚቻለው ከባለስልጣኑ ፈቃድ ሲያገኝ ብቻ መሆኑንም አመላክቷል። መመሪያው ለህዝብ በሽያጭ የኤሌክትሪክ ሃይል ሙሊት አገልግሎት የሚሰጡ ታሪፋቸው በባለስልጣኑ ሲጸድቅላቸው…
Read More
ኢትዮጵያ የስቶክ ማርኬት ገበያን ከ50 ዓመት በኋላ ዳግም አስጀመረች

ኢትዮጵያ የስቶክ ማርኬት ገበያን ከ50 ዓመት በኋላ ዳግም አስጀመረች

ኢትዮጵያ በአጼ ሀይለስላሴ አስተዳድር ዘመን የስቶክ ግብይት የሚፈቅድ ስርዓት የነበራት ቢሆንም በደርግ ዘመን ተቋርጦ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ከ50 ዓመት በኋላ የስቶክ ግብይትን ዳግም ያስጀመረች ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ አስጀምረዋል፡፡ በዚህ የግብይት ስርዓት መሰረት ኩባንያዎች አክስዮኖቻቸውን በይፋ ለገዢዎች መሸጥ የጀመሩ ሲሆን ሸማቾች ደግሞ ለሚገዙት አክስዮን ዋስትና የሚሰጥ ተቋምም ወደ ስራ ገብቷል፡፡ ይህን የአክስዮን ግብይት የሚያሳልጡ ሁለት መንግስታዊ ተቋማት የተቋቋሙ ሲሆን የኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት እና የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ነዋዮች ገበያ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ የስቶክ ግብይትን ከአንድ ዓመት በፊት የመጀመር እቅድ የነበራት ቢሆንም ዘግይቶ ተጀምሯል፡፡ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ስር 39 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው የመንግስት…
Read More
የቻይና ኩባንያዎች ከ300 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን የስራ እድል ፈጥረዋል ተባለ

የቻይና ኩባንያዎች ከ300 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን የስራ እድል ፈጥረዋል ተባለ

ኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ከሳበችው ውስጥ ግማሹ በቻይናዊን የተያዘ እንደሆነ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከቻይና ንግድ ምክር ቤት እና ከቻይና ኢምባሲ ጋር በአዲ አበባ ተወያይተዋል፡፡ ኮሚሽኑ በዚህ ጊዜ እንደገለጸው ባለፉት አምስት አመታት በኢትዮጵያ ከተጀመሩ አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 50 በመቶ የሚሆኑት በቻይና ባለሀብቶች የለሙ ናቸው፡፡ ውይይቱ የቻይና ባለሀብቶችን ለማበረታታት የተዘጋጀ ሲሆን ውይይቱ ለቻይና ባለሀብቶች ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢን ለመፍጠር እና ተጨማሪ ባለሀበቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል፡፡ አሁን ላይ ቻይና በኢትዮጵያ ከ 3 ሺህ 300 በላይ የኢንቨስትመንት ፕሮጀከቶችን በማልማት ላይ ናት የተባለ ሲሆን ቻይና በኢትዮጵያ ከ325 ሺህ በላይ ለሆኑ ኢትዮጵያዊያን የስራ እድሎች ፈጥራለችም ተብሏል፡፡ ከሶስት ወራት በፊት…
Read More
ኢትዮጵያ ከውጪ ንግድ ሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከውጪ ንግድ ሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ባለፉት አራት ወራት ከወጪ ንግድ ከ2 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል፡፡ በተጠቀሱት ጊዜያት ውስጥ 480 ሺህ ቶን የተለያዩ ምርቶችን ወደ ተለያዩ ሀገራት በመላክ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ እንደተገኘ ተገልጿል፡፡ የተገኘው ገቢ ካምናው ተመሳሳይ ወራት ጋር ሲነጻጸር የ947 ሚሊየን ዶላር ብልጫ አሳይቷል ተብሏል፡፡ ከተገኘው አጠቃላይ ገቢ ውስጥ ግብርና 53 ነጥብ 25 በመቶ ድርሻ ሲይዝ ማዕድን 37 በመቶ፣ ማኑፋክቸሪንግ 5 ነጥብ 43 በመቶ እንዲሁም ኤሌክትሪክና ሌሎች 4 ነጥብ 33 በመቶ ድርሻ ይዘዋል፡፡ ወርቅ፣ ቡና፣ ኤሌክትሪክ እና የጥራጥሬ ምርቶች በገቢም ሆነ በመጠን ከዕቅዳችው በላይ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ምርቶች መሆናቸውን የሚስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡ ከተላኩ ምርቶች መካከል 150 ሺህ ቶን…
Read More