19
May
ሚኒስቴሩ በተያዘው በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 649 ቢሊዮን ብር ሰብስቤያለሁ ብሏል ገቢው ከአምናው ተመሳሳይ ጊዜ 74 በመቶ ወይም የ279 ቢሊየን ብር ብልጫ ያለው ነው ተብሏል፡፡ ከተሰበሰበው ገቢ 345.9 ቢሊየን ብሩ ከታክስ የተገኘ ሲሆን ከወጭ ንግድ ቀረጥና ታክስ ደግሞ 307.2 ቢሊየን ብር መሰብሰቡ ተገልጿል። ገቢው በመቶ ቢሊዮኖች ከአምናው ከፍ ያለበት ምክንያት ግን በሪፖርቱ አልተብራራም፡፡ በሌላ በኩል ህገ-ወጥ ንግድ ፣ ገቢን መደበቅ ፣ ግብይትን ያለ ደረሰኝ መከወን ፣ ግብር ስወራና ታክስ ማጭበርበር አሁንም ፈተና ሆነውብኛል ብሏል ሚኒስቴሩ፡፡ ተሰውሮብኝ ነበር ያለውን ገቢ ለማግኘትም በድንገተኛ ፍተሻ ፣ በሒሳብ ምርመራ ወይም ኦዲትና መሰል ስራዎች የህግ ማስከበር ስራ ሰርቻለሁ ብሏል፡፡ በዚህም 7 ሺህ 583 የሒሳብ…