Taxfraud

ከ10 ዓመት በፊት ለተፈጸመ ታክስ ማጭበርበር ቅጣት እንዲጣል የሚፈቅድ ረቂቅ ህግ ተዘጋጀ

ከ10 ዓመት በፊት ለተፈጸመ ታክስ ማጭበርበር ቅጣት እንዲጣል የሚፈቅድ ረቂቅ ህግ ተዘጋጀ

ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ረቂቁ የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ለ10 ዓመታት ወደኋላ በመሄድ ሂሳቡን በመመርመር ወይም ሂሳብ ኦዲት በማድረግ ተጨማሪ ግብር ማስከፈልን ለገቢ ሰብሳቢው የሚፈቅድ ነው፡፡ ዛሬ ለምክር ቤቱ የቀረበው ረቂቅ የግብር አስተዳደር አዋጅ በተለይ ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚደረግ ግብይት ላይ ከፍ ያለ ቅጣትን የሚያስከትሉ አንቀፆችን የያዘ ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ህጋዊ ደረሰኝ ያልሰጠ እንደሆነ በእያንዳንዱ ባልሰጠው ደረሰኝ ልክ 100 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በገንዘብ ይቀጣል ይላል የማሻሽያ አዋጁ ማብራሪያ፡፡ በተጨማሪ ይሄንኑ አስተዳደራዊ ቅጣት በዓመት ሁለት ጊዜ የተቀጣ እንደሆነ እና ሆን ብሎ ድርጊቱን መፈፀሙን ከቀጠለ ድርጊቱ እንደ ወንጀል ጥፋት…
Read More
ደረሰኝ የማይሰጡ ነጋዴዎች የ100 ሺህ ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል ተባለ

ደረሰኝ የማይሰጡ ነጋዴዎች የ100 ሺህ ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል ተባለ

በግብይት ወቅት ማናቸውም ግብር ከፋይ ነጋዴ ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲያከናውን ወይም ዋጋ አሳንሶ የተገኘ በእያንዳንዱ ደረሰኝ የአንድ መቶ ሺህ ብር ቅጣት መጣል የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል። ያለ ደረሰኝ ሲገበያይ የተገኘ ማንኛውም ግብር ከፋይ ለገዢ ባልሰጠው በእያንዳንዱ ደረሰኝ ብዛት ከዚህ ቀደም 50 ሺህ ብር ይቀጣ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ማሻሻያ በተደረገለት የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ መሰረት ወደ አንድ መቶ ሺህ ብር ቅጣት ከፍ ብሏል።የገንዘብ ሚኒስቴር እንደ ዋና ማሻሻያዎች ካነሳቸው መካከል የታክስ የምስክር ወረቀት አሰጣጥን ማሻሻል፣ የታክስ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ በማስታረቅ ሥርዓት መፍታት፣ የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ የሚታረምበትን ሥርዓት ግልጽ ማድረግ፣ እንዲሁም የውሳኔ ማስታወቂያ ማሻሻያና የይግባኝ ማቅረቢያ የጊዜ ገደቦችን በግልጽ ማስቀመጥ የሚሉት ይገኙበታል።እነዚህ…
Read More
ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ

ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ

ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ የስፖርት አወራራጅ ድርጅት ባለቤቶችና ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ገልጿል። መ/ቤቱ ፤ በቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶችና ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር በሚባሉ የገንዘብ ክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተባባሪ ተቋማት ዙሪያ ጥናትና ክትትል ሲከናወን መቆየቱን አመልክቷል። ተጠርጣሪዎቹ ፈቃድ ያላቸውና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በገቡት ውል መሰረት ባለመስራት፣ በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው በመገኘታቸው ፈቃዳቸው የተሰረዘባቸው፣ምንም አይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው በስፖርት አወራራጅነት ተሰማርተው የነበሩ አካላት በዓለም አቀፍ የኢንተርኔት ትስስር አማካይነት በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው ተገኝተዋል ተብሏል። ከፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ለአዲስ አበባና ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ አካላት እንዲሁም በኅብረተሰቡ ትብብር 24 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል ሲል…
Read More