NISS

ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ

ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ

ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ የስፖርት አወራራጅ ድርጅት ባለቤቶችና ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ገልጿል። መ/ቤቱ ፤ በቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶችና ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር በሚባሉ የገንዘብ ክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተባባሪ ተቋማት ዙሪያ ጥናትና ክትትል ሲከናወን መቆየቱን አመልክቷል። ተጠርጣሪዎቹ ፈቃድ ያላቸውና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በገቡት ውል መሰረት ባለመስራት፣ በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው በመገኘታቸው ፈቃዳቸው የተሰረዘባቸው፣ምንም አይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው በስፖርት አወራራጅነት ተሰማርተው የነበሩ አካላት በዓለም አቀፍ የኢንተርኔት ትስስር አማካይነት በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው ተገኝተዋል ተብሏል። ከፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ለአዲስ አበባና ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ አካላት እንዲሁም በኅብረተሰቡ ትብብር 24 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል ሲል…
Read More
በሕገ ወጥ የወርቅ እና የገንዘብ ዝውውር 76 ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገለጸ

በሕገ ወጥ የወርቅ እና የገንዘብ ዝውውር 76 ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገለጸ

በሕገ ወጥ የወርቅ፣ የገንዘብና የጦር መሣሪያ ዝውውር ተሳትፈዋል የተባሉ 76 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡ ፋና እንደዘገበው ከሆነ በተጠቀሱት የወንጀል ድርጊቶች ተሰማርተው በነበሩ የውጭ ሀገር ዜጎችና ኢትዮጵያውያን ላይ አዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ሲዳማ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ክትትል ሲደረግ ቆይቷል ተብሏል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ የወርቅ ማዕድን በሕገ ወጥ መንገድ በማምረት፣ በመሰወርና በማዘዋወር፣ የሀገራችንን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦችን እንዲሁም ሕገወጥ የጦር መሣሪያዎችን በማዘዋወር ወንጀሎች ላይ ተሳታፊ እንደነበሩ መግለጫው ጠቁሟል፡፡ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስና ከየክልሎቹ የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ባካሄደው ልዩ ኦፕሬሽን እስካሁን 45 የውጪ ሀገር ዜጎች እና 31 የሀገር ውስጥ በድምሩ…
Read More