ኢኮኖሚ

የኢትዮጵያ አቪየሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ አደገ

የኢትዮጵያ አቪየሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ አደገ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪዬሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ በማደግ በኤሮስፔስ እና በተለያዩ የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፎች በቅድመ ምረቃ እና ድሕረ ምረቃ ፕሮግራሞች ማስተማር ጀመረ። የአቪዬሽን አካዳሚ የአቪዬሽን ስልጠና ፕሮግራሞችን በአብራሪነት፣ የአውሮፕላን ቴክኒሻን፣ የካቢን ሰራተኛ፣ የአየር መንገድ ሽያጭ እና አገልግሎት እና ሌሎች ስልጠናዎችን ሲሰጥ ቆይቷል።  ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ካደገ በኋላ በኤሮኖቲካል ኢንጂነሪንግ በቢኤስሲ ዲግሪ፣ በአውሮፕላን ጥገና ኢንጂነሪንግ በቢኤስሲ ዲግሪ፣ በአቪዬሽን ማኔጅመንት ቢኤስሲ ዲግሪ፣ በቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ማኔጅመንት ቢኤ ዲግሪ እና ኤምቢኤ በአቪዬሽን ማኔጅመንት የመሳሰሉ የዲግሪ መርሃ ግብሮችን ጀምሯል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው እንደተናገሩት "ከቀጣይ እድገትና ኢንቨስትመንት በኋላ 65 ዓመት ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ማደጉ…
Read More
ዘምዘም ባንክ ከሀገር እና ውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ለመዋሃድ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ዘምዘም ባንክ ከሀገር እና ውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ለመዋሃድ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ዘምዘም ባንክ ከሀገር እና ውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ለመዋሃድ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ የኢትዮጵያ የባንክ ህግ መሻሻሉን ተከትሎ በቅርቡ ወደ አገልግሎት የገባው ዘምዘም ባንክ የተሻለ ገቢ እና ተወዳዳሪ ለመሆን ከሌሎች ባንኮች ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ የባንክ ታሪክ ሙሉ ለሙሉ የእስላሚክ ባንክ አገልግሎትን በመስጠት ቀዳሚ የሆነው ዘምዘም ባንክ ከማንኛውም የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ተዋህዶ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን የባንኩ ፕሩዝዳንት ወይዘሮ መሊካ ለኢትዮ ነጋሪ በድሪ ተናግረዋል፡፡ ፕሬዝዳንቷ አክለውም ዘምዘም ባንክ ስራ ከጀመረበት ሰኔ 2013 ዓ.ም ጀምሮ በ54 ቅርንጫፎቹ በሀገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ባንኩ ሙሉ ለሙሉ ወለድ አልባ የሆኑ ሁሉንም የፋይናንስ አገለግሎቶችን በመስጠት ላይ መሆኑን የተናገሩት…
Read More
የአንድ ኪሎ ሽንኩርት ዋጋ ከሥጋ ከሁለት እጥፍ በላይ የተወደደባት አገር

የአንድ ኪሎ ሽንኩርት ዋጋ ከሥጋ ከሁለት እጥፍ በላይ የተወደደባት አገር

ለምግብ ማጣፈጫነት ከሚውሉ አትክልቶች መካከል ሽንኩርት አንዱ ነው። ሽንኩርት በዓለም ዙሪያ መሠረታዊ የምግብ ግብአቶች ከሆኑት መካከል ይጠቀሳል። በበርካታ አገራት ሽንኩርት በድሃውም ሆነ በሃብታሙም ቤት የሚገኝ የምግብ አካል ሲሆን፣ ሥጋ ደግሞ እንደ ቅንጦት ምግብ የሚታይ ነው። በፊሊፒንስ ግን ይህ በተቃራኒ ሆኗል፤ የሽንኩርት ዋጋ የትኛውንም አይነት ሥጋ ለመግዛት ከሚወጣው ገንዘብ በበርካታ እጥፍ ይበልጣል። ለፊሊፒን ዜጎች ባለፉት ሳምንታት ጊዜ ሽንኩርት መሸመት ቅንጦት ሆኗል። ዋጋው በማሻቀቡ የተነሳ የሽንኩርት መግዣ ከሥጋ መግዣ በእጅጉ ንሯል። በዚህ ሳምንት ፊሊፒንስ ውስጥ አንድ ኪሎ ሽንኩርት 11 ዶላር (600 ብር ገደማ) ሲሆን፣ የአንድ ሙሉ ዶሮ ሥጋ ግን 4 ዶላር (220 ብር ገደማ) ብቻ ነው። የሽንኩርት ዋጋ ንረት የፈጠረውን የገበያ ክፍተት…
Read More
ሩሲያ በክሬሚያ የጦር መሳሪያ ማከማቻ ስፍራ ላይ የደረሰዉ ፍንዳታ በሴራ ነዉ ስትል ተናገረች

ሩሲያ በክሬሚያ የጦር መሳሪያ ማከማቻ ስፍራ ላይ የደረሰዉ ፍንዳታ በሴራ ነዉ ስትል ተናገረች

የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴር በሰሜናዊ ክሬሚያ በሚገኝ ወታደራዊ መጋዘን የደረሰውን ፍንዳታ ተከትሎ ከ3,000 በላይ ሰዎችን አካባቢዉን ለቀው እንዲወጡ ያስገደደ ሲሆን የሴራ ዉጤት ነዉ ሲል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ማስታወቁን የሩሲያ መንግስት ሚዲያ ዘግቧል። በትላንትናዉ እለት የደረሱት ፍንዳታዎች በሜይስኮዬ መንደር አቅራቢያ በሚገኘው የጥይት ማከማቻ ቦታን ያናወጡ እና የባቡር አገልግሎቶችን እንዲሁም የሃይል አቅርቦቶችን ያስተጓጎለ ነበር፡፡ በፍንዳታው በሰው ላይ ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰ ሚኒስቴሩ አክሏል።የሩሲያ ኮምመርሰንት ጋዜጣ በትላንትናዉ እትሙ በክሬሚያ ተጨማሪ ጥቃት ሊፈጸም እንደሚችል ዘግቧል፡ እማኞችን ጠቅሶ እንደዘገበው በግቫርዴስኮዬ ባሕረ ገብ መሬት ላይ በሚገኘው የሩሲያ ወታደራዊ አየር ማረፊያ ላይ ጭስ መታየቱን ጽፏል፡፡ባለፈው ሳምንት በክሬሚያ በሩሲያ ስር በሚተዳደረው የአየር ጣቢያ ላይ የደረሰ ፍንዳታ የነበረ ሲሆን ሞስኮ በወቅቱ…
Read More
የሮበርት ሙጋቤ ልጅ ድግስ ላይ ንብረት አውድሟል ተብሎ ታሠረ

የሮበርት ሙጋቤ ልጅ ድግስ ላይ ንብረት አውድሟል ተብሎ ታሠረ

የቀድሞው የዚምባብዌ ፕሬዝደንት ሮበርት ሙጋቤ ወንድ ልጅ ሃራሬ ውስጥ በተዘጋጀ ድግስ ላይ ንብረት አውድሟል ተብሎ በቁጥጥር ሥር ዋለ። 31 ዓመቱ እንደሆነ የሚገመተው ሮበርት ሙጋቤ ጁኒዬር ሶስት ንብረት የማውደም እና ሁለት ፖሊስ የመተናኮስ ክስ ቀርቦበታል ሲሉ ጠበቃቸው ተናግረዋል። በድግሱ ላይ የመኪናዎች መስታወት ሲረግፍ አንድ የፖሊስ መኮንን ላይ ምራቅ መተፋቱ ተሰምቷል። የሙጋቤ ልጅ የቀረበበትን ክስ አጣጥሎ ከደሙ ንፁሕ ነኝ ይላል። አሁን ከእሥር ተለቆ ክሱን በድርድር ለመፍታት እየጣረም እንደሆነ ተነግሯል። ፖሊስ በትዊተር ገፁ እንደገለጠው የሮበርት ሙጋቤ ልጅ ጓደኛ የሆነው ሲንዲሶ ንካታዞ ያቀረበውን ቅሬታ ተከትሎ ነው ፖሊስ ወደ ሥፍራው ያቀናው። በድግሱ ላይ የደረሰው የንብረት ውድመት በገንዘብ ሲሰላ 12 ሺህ ዶላር አካባቢ ሊደርስ እንደሚችል ፖሊስ…
Read More
በወልቂጤ ግድያ የፈጸሙ የፀጥታ ኃይሎች በሕግ ይጠየቁ በሚል ነዋሪዎች አድማ መቱ

በወልቂጤ ግድያ የፈጸሙ የፀጥታ ኃይሎች በሕግ ይጠየቁ በሚል ነዋሪዎች አድማ መቱ

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የውሃ አቅርቦት ችግር እንዲፈታ እና የውሃ ጥያቄያቸውን ለማቅረብ አደባባይ በወጡ ሰልፈኞች ላይ የተኮሱ የፀጥታ ኃይሎች ለፍርድ እንዲቀርቡ በመጠየቅ ከቤት ያለመውጣት አድማ መምታታቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። ከቤት ያለመውጣት አድማው ከተጀመረ ቀናት መቆጠራቸውን የተናገሩት ነዋሪዎች የከተማዋ እንቅስቃሴም ሙሉ በሙሉ ተገድቧል ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በከተማዋ ለወራት የተቋረጠው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር እንዲፈታ ለመጠየቅ ባለፈው ሳምንት ጄሪካን ይዘው አደባባይ በወጡ ሰልፈኞች ላይ የፀጥታ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ ሦስት ሰዎች መገደላቸውን እና ቢያንስ 30 ሰዎች የአካል ጉዳት መድረሱን ነዋሪዎች እና ኢሰመኮ ማስታወቃቸው ይታወሳል። በከተማዋ ትራንስፖርት፣ የባንክ አገልግሎት፣ የመገበያያ መደብሮችም ሆነ የትኞቹም የመንግሥት ተቋማት ተዘግተው ከተማዋ ጭር ብላ መሰንበቷን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ሰኞ ምሽት…
Read More