ኢኮኖሚ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኮፐንሀገን ወደ አዲስ አበባ የካርጎ አገልግሎት ጀመረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኮፐንሀገን ወደ አዲስ አበባ የካርጎ አገልግሎት ጀመረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኮፐንሀገን ወደ አዲስ አበባ የካርጎ አገልግሎት ጀመረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዴንማርክ  ኮፐንሀገን ወደ አዲስ አበባ ሳምንታዊ  የእቃ ጭነት አገልግሎት በረራ ጀመረ።  የእቃ ጭነት በረራው  የሚደረገው  በቅርቡ ከመንገደኛ ወደ እቃ ጭነት አገልግሎት በተቀየረው ቦይንግ 767-300F አውሮፕላን እንደሆነ ተገልጿል። በዚህ ሳምንታዊ እያንዳንዱ በረራ እስከ 45 ቶን ያህል ጭነት እንደሚጓጓዝ አየር መንገዱ ለኢትዮ ነጋሪ ገልጿል። ይህ አዲስ የእቃ ጭነት  አገልግሎት በአውሮፓ  እና በተቀረው  ዓለም መካከል  ያለውን የንግድ  እንቅስቃሴ የሚያሳልጥ ይሆናል ተብሏል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመጪው ግንቦት ወር  ጀምሮ ወደ ኮፐንሀገን  የመንገደኛ በረራ  አገልግሎት እጀምራለሁ ብሏል። ይህ የመንገደኞች በረራ መጀመርም ተጨማሪ  የካርጎ  አገልግሎት አቅም ይፈጥርልኛል ብሏል። ይህ በዚህ እንዳለ የኢትዮጵያ አየር መንገድ  ወደ  ኢንዶኔዢያ ዋና ከተማ ኩዋላላፑር ከተማ አዲስ በረራ እንደሚጀምር አስታውቋል። አየር መንገዱ ከመጋቢት 24,…
Read More
ኢትዮጵያ ወደ አግዋ የመመለስ እድል አላት?

ኢትዮጵያ ወደ አግዋ የመመለስ እድል አላት?

በሰሜን ኢትዮጵያ በፌደራል መንግሥት እና ህወሀት መካከል ጦርነት መጀመሩን ተከትሎ ነበር አሜሪካ ኢትዮጵያን ከአሜሪካ የንግድ ችሮታ (አግዋ) እድል ያገደችው። የእግዱ ዋነኛ ምክንያትም በጦርነቱ ምክንያት በዜጎች ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እየተፈጸሙ ነው የሚል ሲሆን ኢትዮጵያ የአሜሪካንን ውሳኔ ተቃውማም ነበር። የአግዋ እድል መሰረዝ በተለይም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ባሉ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የተቀጠሩ ዜጎችን ስራ አጥ በማድረግ በጦርነቱ ምንም አይነት ተሳትፎ የሌላቸው ኢትዮጵያዊያንን ይጎዳል ስትል ኢትዮጵያ አሜሪካ ውሳኔዋን እንድታጤነው ጠይቃም ነበር። ይሁንና ዋሸንግተን ኢትዮጵያን ከአግዋ እግድ እስካሁን ያላነሳች ሲሆን የመነሳት እድል ይኖራት ይሆን የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው። ጥያቄው በተለይም የጦርነቱ ዋነኛ ተሳታፊዎች የሆኑት የፌደራል መንግሥት እና ህወሀት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል 331 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ ድጋፍ የሚውል 331 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

አሜሪካ ለኢትዮጵያ ከ331 ሚሊየን ዶላር በላይ የሰብአዊ ድጋፍ ይፋ አደረገች። ለሥራ ጉብኝ አዲስ አበባ የሚገኙት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ለኢትዮጵያ ከ331 ሚሊየን ዶላር በላይ የሰብአዊ ድጋፍ ይፋ አድርገዋል። አንቶኒ ብሊንከን እንዳስታወቁት ድጋፉ በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እና በአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት አማካኝነት የሚሸፈን ነው፡፡ ድጋፉም በተለያዩ ምክንያቶች በችግር ለተጋለጡ ወገኖች ለምግብ፣ ለመድሃኒት፣ ለንጹህ የመጠጥ ውሃ የሚውል መሆኑን ገልፀዋል። ይህም በግጭት ለተጎዱ፣ ለተፈናቀሉ፣ በድርቅ ለተጠቁ እና ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ዜጎች ሕይወት አድን ድጋፍ ማድረግ ያስችላል ተብላል።
Read More
በአዲስ አበባ የቡና አፈላል አውደ ርዕይ ሊዘጋጅ እንደሆነ ተገለጸ

በአዲስ አበባ የቡና አፈላል አውደ ርዕይ ሊዘጋጅ እንደሆነ ተገለጸ

በአዲስ አበባ የቡና አፈላል አውደ ርዕይ ሊዘጋጅ እንደሆነ ተገለጸ የኢትዮጵያዊያን ባህል ለማስተዋወቅ ዋና ዓላማው ያደረገ የኢትዮጵያ ቡቡና አፈላል ሂደትን እና ተያያዥ ባህልን የሚያሳይ አውደ ርዕይ እንደሚዘጋጅ ተገልጿል። በዋርካ ኮፊ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት አማካኝነት የተዘጋጀው ይህ አውደ ርዕይ የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 9 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል ይዘጋጃል ተብሏል። የድርጅቱ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሰዓዳ ሙስጠፋ በአውደ ርዕዩ ዝግጅት ዙሪያ በሰጡት መግለጫ "በዝግጅቱ ላይ የኢትዮጵያ ቡና አቆላል፣ አጠጣጥ እና ተያያዥ ባህሎች ለታዳሚያን ይቀርባል" ብልዋል። በዝግጅቱ ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ መጋበዙን የሚናገሩት ወይዘሮ ሰዓዳ የኢትዮጵያን ቡና በመግዛት የሚታወቁ ሀገራት አምባሳደሮች እና ሌሎችም በእንግድነት እንደሚገኙም ጠቁመዋል። ከአዲስ አበባ ባህልና…
Read More
መንግሥት ለአዲስ አበባ አመራሮቹ ለሞባይል ስልክ 140 ሺህ ብር ፈቀደ

መንግሥት ለአዲስ አበባ አመራሮቹ ለሞባይል ስልክ 140 ሺህ ብር ፈቀደ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለአመራሮች የእጅ ስልክ መግዣ 140 ሺህ ብር ድረስ ፈቀደ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በጥር ወር ላይ በወሰነዉ ዉሳኔ መሰረት፣ ለከተማዋ አመራሮች የሞባይል ስልክ ቀፎ ግዢ መፍቀዱ ተገልጿል። በዚህም መሰረት ለከንቲባ እና ለከተማ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ 140 ሺህ ብር ተመድቧል። ለምክትል ከንቲባ፣በምክትል ከንቲባ ማዕረግ ደረጃ ለተሿሙ አመራሮች እና ለምክትል አፈ-ጉባኤ ስልክ መግዣ 120 ሺህ ብር መወሰኑንም ሰምተናል ሲል ኢትዮ ኤፍ ዘግባል። ለክፍለ ከተማ 50 ሺህ ፣ለወረዳ ዋና ስራ አስፈፃሚ የ40 ሺህ እንዲሁም ለወረዳ ቀሪ አመራሮች 30 ሺህ ብር የሚያወጣ የሞባይል ስልክ እንዲገዛላቸዉ ተፈቅዷል። ይህንን የሚያስፈፅም ደብዳቤም በየክፍለ ከተማዎችና ወረዳዎች ጭምር እንደተበተነ ተገልጿል።
Read More
<strong>ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመቋረጧ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተገለጸ</strong>

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመቋረጧ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተገለጸ

በሳሙኤል አባተ ኢትዮጵያ በኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተገልጻል። ቶፕ 10 ቪፒኤን የቴክኖሎጂ ኩባንያ እንዳስታወቀው፣ በትግራይ ክልል የነበረውን ጦርነት ተከትሎ ለአንድ አመት ሙሉ የኢንተርኔት አገልግሎት በመዘጋቱ ሃገሪቱ 146 ሚሊዮን ዶላር ማጣቷን አስታውቋል። አሁንም ቢሆንም በመላው ሀገሪቱ ኢንተርኔት በመቋረጡ ሚሊዮን ዶላሮችን እያጣች ትገኛለች ብሏል። ኢንተርኔት ከተዘጋ አንድ ወር ያለፈ ሲሆን መንግሥት እስካሁን ስለጉዳዩ ያለው ነገር የለም። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ሚዲያ ምክር ቤት እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት የኢትዮጵያ መንግሥት ኢንተርኔት እንዲከፍት ጠይቀዋል። በአሁኑ ወቅት የኢንተርኔት ገደብ የተደረገባቸው ፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ቲክቶክ እና ዩቲዩብ  ገደብ የተደረገባቸው የትስስር ገጾች ናቸው። ኢትዮጵያ ከዚህ በፊትም የኢንተርኔት ገደብ በመጣል የምትታወቅ ሲሆን በተለይም…
Read More
ሩሲያ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፖለቲካዊ ቅርጽ ማስያዝ ተገቢ አለመሆኑን ገለጸች

ሩሲያ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፖለቲካዊ ቅርጽ ማስያዝ ተገቢ አለመሆኑን ገለጸች

ሩሲያ የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፖለቲካዊ ቅርፅ ማስያዝ ተገቢ አለመሆኑን አስታወቀች፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ  ግድብ  የልማት  ጉዳይ ሆኖ ሳለ  ፖለቲካዊ ይዘት  እንዲኖረዉ የሚደረግ ጥረትን እንደምትቃወም ነው ሩሲያ ያስታወቀችው፡፡ በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር የቭግኒ  ትረኪን  ከኢትዮ ኤፍ ኤም ጋር በነበራቸው ቀይታ፤በግድቡ ላይ መንግስታቸዉ  ነፃና ገለልተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሞስኮ ከኢትዮጵያ፤ከሱዳንና ከግብጽ ጋር መልካም ግንኙነት እንዳላት የገለፁት  አምባሳደሩ፤ግድቡን የፖለቲካ ጉዳይ ለማድረግ  የሚደረገዉን ጥረት  እንደማትቀበል አስታዉቀዋል፡፡ በዚህም ሩሲያ  የግድቡ የድርድር ሂደት ወደ ፀጥታዉ ምክር ቤት  ባመራበት ወቅት መቃወሟን አስታዉሰዋል፡፡የሩሲያ መንግስት  የኢትዮጵያን  የልማት እቅድ እንደሚደግፍም ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም ሶስቱ ሀገራት በግዱቡ ዙሪያ ያላቸዉን አለመግባባት በሰላማዊ መንገድ  እንዲፈቱ  በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር  የቭገኒ ትረኪን ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ የግድቡ ግንባታ 88…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የጣለችውን የእርዳታ እቀባ እንደምታነሳ ገለጸች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የጣለችውን የእርዳታ እቀባ እንደምታነሳ ገለጸች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የጣለችውን የፋይናንስ ድጋፍ እቀባ ልታነሳ መሆኑ ተዘገበ ለሁለት ዓመታት ሲካሄድ ቆይቶ በተያዘው ዓመት ጥቅምት ወር መቋጫ ባገኘው የፌዴራል መንግሥት እና ሕወሓት ጦርነት ከመንግሥት ጋር ቅራኔ ውስጥ ገብቶ የቆየው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የቆየውን የእርዳታ እና የፋይናንስ ድጋፍ እቀባ ሊያነሳ መሆኑን መስማቱን የዘገበው ፎሬን ፖሊሲ ነው፡፡ መጽሔቱ ከባለሥልጣናት ሰምቼዋለሁ ባለው መረጃ መሠረት የባይደን አስተዳደር እቀባውን ማንሳቱን በቅርቡ አዲስ አበባ ያቀናሉ በተባሉት የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኃላፊ አንቶንዮ ብሊንክን በኩል ይፋ ያደርጋል፡፡ በሰሜኑ ጦርነት ተደጋጋሚ መግለጫዎችን ስታወጣ የቆየችውና በመንግሥት እና ሕወሓት የሠላም ስምምነት ሒደት ከፍተኛ ሚና የነበራት አሜሪካ፤ ጦርነቱ በተጀመረበት 2013 ግንቦት ወር ላይ ነበር…
Read More
መንግሥት በማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ በድጋሚ ተጠየቀ

መንግሥት በማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ በድጋሚ ተጠየቀ

የኢትዮጵየ መንግሥት ፌስቡክ እና ዩቲዩብን ጨምሮ በማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ የጠየቀው ዓለም አቀፉ መብቶች ተሟጋች አምነስቲ ኢንተርናሽናል ነው፡፡  አምነስቲ የማኅበራዊ መገናኛ መድረኮቹ ከተገደቡ አንድ ወር እንደሞላቸው ዛሬ ሐሙስ የካቲት 30፣ 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ላይ አስታውቋል፡፡  በጉዳዩ ላይ የተናገሩት የአምነስቲ የምሥራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር ፍላቪያ ምዋንጎቪ፤ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ቲክቶክ እና ዩቲዩብን ማኅበረሰቡ እንዳይጠቀም ገደብ ከጣሉ አንድ ወር እንደሞላቸው አስታውሰው፤ ይህም ‹‹የዜጎችን ሃሳብን በነጻነት የመግለጽና መረጃን የማግኘት መብቶችን በግልጽ የሚጥስ ነው›› ብለዋል፡፡  በኢትዮጵያ አምነስቲ የጠቀሳቸው የማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ገደበ የተጣለባቸው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ የተፈጠረ ክስተት ተከትሎ ውጥረት በመስፈኑ ነበር፡፡  የመብቶች ተሟጋቹ በመግለጫው…
Read More
<strong>በኢትዮጵያ 22 ሚሊዮን ሴቶች የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ እንደማያገኙ ተገለጸ</strong>

በኢትዮጵያ 22 ሚሊዮን ሴቶች የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ እንደማያገኙ ተገለጸ

በኢትዮጵያ 22 ሚሊዮን ሴቶች የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ እንደማያገኙ ተገለጸ በኢትዮጵያ ባለፉት ጊዜያት የተከሰቱ ሰው ሰራሽ የተፈጥሮ ችግሮች የተነሳ ቁጥራቸዉ ከፍተኛ የሆኑ ዜጎች ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ ምክንያት መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ ጋር ተያይዞ በሚነሱ ችግሮች በከፍተኛ ሁኔታ ሰላባ የሚሆኔት ሴቶች መሆናቸውን ጥናቶች ያመላክታሉ።ይህንኑ ተከትሎ በኢትዮጵያ የወር አበባ ከሚያዩ ከ35 ሚሊዮን በላይ ሴቶች ውስጥ 22 ሚሊዮን ያህሉ የወር አበባ ንጽሕና መጠበቂያ እንደማያገኙ የአደይ የሚታጠብ ንጽሕና መጠበቂያ መሥራች ወይዘሮ ሚካል ማሞ ተናግረዋል። 22 ሚሊዮን ያህሉ ምንም አይነት ስለ ንጽህና መጠበቂያ መረጃ የማያገኙ መሆናቸውን የሚያስረዱት ሚካል ይህዉ ቁጥር በቀጣይ ሊያሻቅብ እንደሚችል ስጋታቸዉን ገልጸዋል።ይህንን አስመልክቶ የአደይ የሚታጠብ ንጽሕና መጠበቂያ ድርጅት ዘላቂ የንጽህና መጠበቂያ ምርቶችን በማምረት ላይ…
Read More