AGOA

ኢትዮጵያ ከተመድ የ28 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ አገኘች

ኢትዮጵያ ከተመድ የ28 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ አገኘች

የተገኘው በጀት የጨርቃጨርቅና አልባሳት ኢንዱስትሪን ምርታማነት ለማሳደግ እና ለማዘመን እንደሚውል ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) የጨርቃጨርቅና አልባሳት ኢንዱስትሪን ለማልማት የሚያስችል የ28 ሚሊየን ዶላር ሥምምነት ተፈራርመዋል። ሥምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና የዩኒዶ የኢትዮጵያ ተወካይ ካልባሮ አውሬሊያ ፓትሪዚያ ተፈራርመውታል። ፕሮጀክቱ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ልማት ኢንስቲትዩት በኩል የሚተገበር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል። በተጨማሪም የዘርፉን ኢኮኖሚ ለማስተዋወቅና የቴክኖሎጂ ልማትን ለማሳደግ እንዲሁም የሚለቀቁ ተረፈ ምርቶችን በመቀነስ መልሶ ጥቅም ላይ ማዋል የሚያስችሉ ሥራዎችን ለመተግበር እንደሚያስችልም በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል። ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሀገራት መካከል አንዷ የነበረች ቢሆንም ባለፉት ዓመታት ውስጥ በጦርነት ውስጥ መቆየቷ…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ ከሁለት ዓመት በፊት የተቀሰቃሰው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የአሜሪካንን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ይጎዳል በሚል ነበር ጦርነቱ እንዲቆም ጫና ስታደርግ የቆየችው፡፡ ይህ ጦርነት ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ምስራቅ አፍሪካን ይጎዳል የምትለው አሜሪካ ጦርነቱ እንዲቆም የተለያዩ ጫናዎችን ያደረገች ሲሆን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈጽሟል በሚል የተለያዩ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች፡፡ በዋሸንግተን ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል በኢትዮጵያ ላይ ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ ማዕቀብ የሚባል ሲሆን በፈረንጆቹ መስከረም 2021 ላይ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ማዕቀብ ተጥሏል፡፡ ይህ ማዕቀብ ከአንድ ሳምንት በኋላ የሚጠናቀቅ ቢሆንም ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ማዕቀቡ ለተጨማሪ አንድ ዓመት እንዲራዘም መፈረማቸውን አስታውቀዋል፡፡ አሜሪካ ማዕቀቡን ለአንድ ዓመት ያራዘመችው በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ አሁንም ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለምስራቅ አፍሪካ እና ለአሜሪካ የውጭ ጉዳዮች ፖሊሲ…
Read More
የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ የዘጠኝ ወራት የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ። የንግድ እና ቀጠናዊ ውህደት ሚንስቴር እንደገለጸው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከወጪ ንግድ 3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ ነበር። ይሁንና የተገኘው ገቢ ግን በአንድ ቢሊዮን ዶላር ቀንሶ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል ተብሏል። ለገቢው መቀነስ የጸጥታ ችግሮች፣ ህገወጥ ንግድ፣ የዓለም ንግድ መቀዛቀዝ እና የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት በምክንያትነት ተጠቅሰዋል። ከተገኘው ገቢ ውስጥም ግብርና የ77 በመቶ ድርሻ ሲያዝ ቀሪው ማዕድን፣ ኢንዱስትሪ እና ኤሌክትሪክ ሽያጭ እንደሆኑ ሚንስቴሩ ገልጿል ባለፉት ሁለት ዓመታት በጦርነት ውስጥ የቆየችው ኢትዮጵያ የወጪ ንግዷ ተዳክሞ የቆየ ሲሆን በአሜሪካ የተጣለባት ማዕቀብ፣ ህገወጥ የማዕድን ገበያ መስፋፋት ለወጪ ንግዱ ዋነኛ ችግሮች…
Read More
ኢትዮጵያ ወደ አግዋ የመመለስ እድል አላት?

ኢትዮጵያ ወደ አግዋ የመመለስ እድል አላት?

በሰሜን ኢትዮጵያ በፌደራል መንግሥት እና ህወሀት መካከል ጦርነት መጀመሩን ተከትሎ ነበር አሜሪካ ኢትዮጵያን ከአሜሪካ የንግድ ችሮታ (አግዋ) እድል ያገደችው። የእግዱ ዋነኛ ምክንያትም በጦርነቱ ምክንያት በዜጎች ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እየተፈጸሙ ነው የሚል ሲሆን ኢትዮጵያ የአሜሪካንን ውሳኔ ተቃውማም ነበር። የአግዋ እድል መሰረዝ በተለይም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ባሉ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የተቀጠሩ ዜጎችን ስራ አጥ በማድረግ በጦርነቱ ምንም አይነት ተሳትፎ የሌላቸው ኢትዮጵያዊያንን ይጎዳል ስትል ኢትዮጵያ አሜሪካ ውሳኔዋን እንድታጤነው ጠይቃም ነበር። ይሁንና ዋሸንግተን ኢትዮጵያን ከአግዋ እግድ እስካሁን ያላነሳች ሲሆን የመነሳት እድል ይኖራት ይሆን የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው። ጥያቄው በተለይም የጦርነቱ ዋነኛ ተሳታፊዎች የሆኑት የፌደራል መንግሥት እና ህወሀት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት…
Read More