AddisAbaba

ኤም-ፔሳ ኢትዮጵያ በአማራ ክልል ግብር የድጅታል ገንዘብ አገልግሎት ለመስጠት ተስማማ

ኤም-ፔሳ ኢትዮጵያ በአማራ ክልል ግብር የድጅታል ገንዘብ አገልግሎት ለመስጠት ተስማማ

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የታክስ ክፍያዎችን በኤም-ፔሳ የዲጂታል ስርዓት ለመሰብሰብ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎት አቅራቢ በሆነው ኤምፔሳ_ኢትዮጵያ እና የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ መካከል በባህር ዳር ከተማ ተፈርሟል። ግብር ከፋዮች ከዚህ በኋላ ኤም-ፔሳን በመጠቀም ግብራቸውን ካሉበት ሆነው በዲጂታል አማራጭ በቀላሉ መክፈል ይችላሉ ተብሏል። ከ477 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮች ያሉት የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2017 የግብር ዘመን 67 ቢሊየን ብር መሰብሰብ መቻሉን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር) ተናግረዋል። በ2018 በጀት ዓመትም ክልሉ 100.37 ቢሊየን ብር የመሰብሰብ እቅድ ያለው ሲሆን ከዚህ ውስጥ እስካሁን 60 በመቶ የሚሆነውን ሰብስቧል ብለዋል። የታቀደውን ገቢ መሰብሰብ የሚቻለው በዲጂታል አማራጭ በመታገዝ ግብርን በቀላሉና…
Read More
በአዲሱ የነዳጅ አቅርቦት መመሪያ መሰረት ቅድሚያ የሚሰጣቸው እነማን ናቸው?

በአዲሱ የነዳጅ አቅርቦት መመሪያ መሰረት ቅድሚያ የሚሰጣቸው እነማን ናቸው?

የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለሥልጣን በመካከለኛው ምስራቅ ያጋጠመውን ጦርነት ተከትሎ ዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተውን የነዳጅ አቅርቦት መስተጓጎል ለመቋቋም በአገር ውስጥ የነዳጅ ስርጭት እና ግብይት ላይ ጥብቅ የቁጠባ እርምጃዎች እንዲወሰዱ የሚያዝ አዲስ መመሪያ አውጥቷል። በመመሪያው መሠረት የነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች ለማንኛውም የነዳጅ ዓይነት አቅርቦት ቅድሚያ እንዲሰጡ ያላቸውን አካላት ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት ለፀጥታ ተቋማት፣ ቁልፍ ለሆኑ የመንግስት ፕሮጀክቶች እና በተለይም በመጠናቀቅ ላይ ላሉ የልማት ስራዎች ቅድሚያ እንዲሰጣቸው አዟል። ለኢንዱስትሪዎች፣ መሠረታዊ ሸቀጦችን ለሚያመርቱ አምራች ድርጅቶች እና ምርታቸውን ወደ ውጭ ለሚልኩ ተቋማትም ቅድሚያ እንዲሰጣቸው ከተባሉ አካላት መካከል ናቸው። እንዲሁም ከፍተኛ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለሚታይባቸው እና የሀገር አቋራጭ የትራንስፖርት ፍሰት ላለባቸው የኮሪደር አካባቢዎች እና ለሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች…
Read More
ኢትዮጵያ የ4 ቢሊዮን ዶላር ማዕድን ኢንቨስትመንት ተፈራረመች

ኢትዮጵያ የ4 ቢሊዮን ዶላር ማዕድን ኢንቨስትመንት ተፈራረመች

በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው እንደሆነ የተገለጸ የብረን ማዕድን በኦሮሚያ ክልል ወለጋ ጊምቢ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ለማውጣት ስምምነት ተፈርሟል፡፡ የማዕድን ሚኒስቴር በኢትዮጵያ እና ቻይናዊያን በተቋቋሙ ኩባንያዎች መካከል የብረት ማዕድን ልማት ፕሮጀክት ዛሬ ተፈራርሟል፡፡ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ አለው የተባለው ይህ የ10 ዓመት የብረት ማዕድን ማውጣት ስምምነት የማዕድን ሚኒስቴር እና ዜድ ዋይ ቲቢ-ዲኤይኤም ስቲል ማኑፋክቸሪንግ ከተሰኘ የግል ኩባንያ ጋር ስምምነት ፈጽሟል፡፡ የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ ከስምምነቱ በኋላ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የብረት ማዕድናት እንዳሏት ካወቀች ከ70 ዓመት በላይ ቢሆናትም “እስካሁን አንድም የብረት ማዕድን አለማውጣቷን” ተናግረዋል፡፡ “በወለጋ ጊምቢ ቢቂላል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ብረት እንዳለን የታወቀው በ1956 ነበር፣ ግን እንደምታውቁት እስካሁን አንድም ብረት ማዕድን…
Read More
በጋሞ ዞን ባጋጠመ የመሬት መንሸራተት አደጋ የሟቾች ቁጥር 107 መድረሱ ተገለጸ

በጋሞ ዞን ባጋጠመ የመሬት መንሸራተት አደጋ የሟቾች ቁጥር 107 መድረሱ ተገለጸ

‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ፣ካምባ እና ቦንኬ በተባሉ ወረዳዎች በደረሰው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 107 መድረሱን የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) ተናግረዋል። ‎ከሟቾቹ መካከል ከጋጮ ባባ ወረዳ ብቻ 102፣ ከካምባ ወረዳ 2 እንዲሁም ከቦንኬ ወረዳ 3 በድምሩ የ107 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አስተዳዳሪው ገልጸዋል። አስተዳዳሪው አክለውም እስካሁን በተከናወነው አስቸጋሪ ፍለጋ የ57 ሰዎች አስክሬን መገኘቱንና በጋጮ ባባ ወረዳ የቀሪ 50 ሰዎች አስክሬን እየተፈለገ መሆኑን ተናግረዋል። ‎የአከባቢው መልካምድር አስቸጋሪ መሆን አስክሬን ፍለጋውን ከባድ ማድረጉን የገለፁት የዞኑ አስተዳዳሪው ጉዳት ለደረሰባቸውና ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ የዕለት እርዳት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል። ‎የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በበኩሉ የአደጋ መከታተያ…
Read More
የእስራኤል- ኢራን ጦርነት ለነዳጅ ድጎማ የሚወጣውን ገንዘብ ጨምሮታል ተባለ

የእስራኤል- ኢራን ጦርነት ለነዳጅ ድጎማ የሚወጣውን ገንዘብ ጨምሮታል ተባለ

ኢትዮጵያ ለነዳጅ ግዢ በየዓመቱ ከ4 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ወጪ እንደምታደርግ ተገልጿል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ዛሬ መጋቢት 2፣ 2018 በሰጡት መግለጫ በእስራኤል-አሜሪካ እና ኢራን መካከል በተጀመረው ጦርነት ምክንያት ለነዳጅ ድጎማ የሚያወጣው ወጪ እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ አህመድ ገለጻ ይህ ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ኢትዮጵያ አንድ ሊትር ቤንዚን በ129 ብር ለተጠቃሚዎች ስታቀርብ የነበረ ሲሆን ድጎማው ቢቀር ግን የአንድ ሊትር ቤንዚን መሸጫ ዋጋ 157 ብር ይሆን ነበር፡፡ እንዲሁም ነጭ ናፍጣ 129 ነበር በሊትር ሲሸጥ ነበር የተባለ ሲሆን ድጎማው ቢነሳ 182 ነጥብ 8 ብር መሸጥ ነበረበት ተብሏል፡፡ ሚኒስትሩ አክለውም በመካከለኛው ምስራቅ የተጀመረው ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ኢትዮጵያ ቤንዚን የ28 ነጥብ…
Read More
የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን 60 ሰራተኞቹ እንደተገደሉበት አስታወቀ

የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን 60 ሰራተኞቹ እንደተገደሉበት አስታወቀ

የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ባለፉት 60 ዓመታት ቢያንስ 60 ሠራተኞቹን በሥራ ላይ እያሉ ህይወታቸውን እንዳጡ ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ባለፉት 6 አሥርት ዓመታት የዱር እንስሳትን እና የተፈጥሮ ሀብትን በመጠበቅ ሂደት ውስጥ ቢያንስ 60 ሠራተኞቹ በሥራ ላይ እያሉ ሕይወታቸውን ማጣታቸውን አስታውቋል። ባለሥልጣኑ ዛሬ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የ60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን የፊታችን መጋቢት 3 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚያከብር አስታውቋል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጅራ፣ ሠራተኞቹ ሕይወታቸውን ያጡት ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጋር በተያያዙ የተለያዩ የሥራ ላይ ፈተናዎች መሆኑን ገልጸዋል። ባለሥልጣኑ ባለፉት 60 ዓመታት ውስጥ ከ1 ሺህ 700 በላይ ለሚሆኑ ልዩ ልዩ የዱር እንስሳት ዝርያዎች ጥበቃ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሴት ፓይለቶች ቁጥር 95 መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሴት ፓይለቶች ቁጥር 95 መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (ማርች 8) በማስመልከት፣ በሴቶች ባለሙያዎች ብቻ የሚመሩ 8 በረራዎችን በተመሳሳይ ጊዜ ወደ ተለያዩ የአለም ሀገራትና የሀገር ውስጥ መዳረሻዎች እንደሚያከናውን ገልጿል። አየር መንገዱ ዕለቱን በማስመልከት ባከናወነው መርሃግብር ላይ እንደገለጸው ወደ ካይሮ፣ ጅቡቲ፣ ናይሮቢ፣ ፍራንክፈርት፣አክራ፣ ሙምባይ፣ ዊንድሆክ እና ድሬዳዋ የሚደረጉ በረራዎች ሙሉ በሙሉ በሴት ፓይለቶች፣ ቴክኒሻኖች እና የበረራ አስተናጋጆች የሚመሩ ይሆናሉ ተብሏል። ይህ ልዩ የበረራ መርሃ ግብር ሴቶች በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ ያላቸውን አቅምና ተሳትፎ ለማሳየት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ገልጸዋል። እንደ ዋና ስራ አስፈጻሚው መረጃ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ካሉ ጠቅላላ ሰራተኞች መካከል 40 በመቶ ያህሉ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሳምንት የ137 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እያስተናገደ መሆኑን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሳምንት የ137 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እያስተናገደ መሆኑን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በእስራኤል-ኢራን ጦርነት ምክንያት በሳምንት የ137 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እያስተናገደ መሆኑን ገለጸ ከሰባት ቀናት በፊት የተጀመረው የእስራኤል-ኢራን ጦርነት ጉዳቱ በመላው ዓለም ላይ ሲሆን ኢትዮጵያም የጦርነቱ ተጎጂ ሆኗ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንዳስታወቀው በዚህ ጦርነት ምክንያት በየሳምንቱ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የካርጎ በረራን ሳይጨምር የመንገደኞችን ብቻ 101 በላይ በረራዎችን እየሰረዘ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በረራዎቹ በመሰረዛቸው ምክንያትም እስከ 137 ሚሊዮን ዶላር በማጣት ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡ አየር መንገዱ የእስራኤል- ኢራን ጦርነት ከመጀመሩ በፊት በቀን ወደ ዱባይ ሦስት ጊዜ ፣ ወደ ሻርጃ አንድ ጊዜ፣ ወደ እስራኤል ሦስት ጊዜ፣ ወደ አቡዳቢ፣ ወደ አማን ሁለቴ መንገደኞችን ያመላልስ ነበር። በጦርነቱ ምክንያት አየር መንገዱ በአማካኝ በየዕለቱ 15…
Read More
አንድ የአሜሪካ ዶላር ዋጋ ወደ 156 ብር ከፍ ማለቱ ተገለጸ

አንድ የአሜሪካ ዶላር ዋጋ ወደ 156 ብር ከፍ ማለቱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባከናወነው 20ኛው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ አንድ የአሜሪካ ዶላርን አማካይ በ155 ነጥብ 4 ብር መድረሱን ይፋ አድርጓል። ብሔራዊ ባንክ ለገበያ ያቀረበው የውጭ ምንዛሬ መጠን 70 ሚሊዮን ዶላር ቢሆንም፣ ከንግድ ባንኮች በኩል የቀረበው የፍላጎት መጠን ግን 177 ነጥብ 12 ሚሊዮን ዶላር ሆኖ ሆኗል። ይህም አቅርቦቱ ከፍላጎቱ ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ልዩነት እንዳለው ያሳያል። ከፍተኛው የማሸነፊያ ዋጋ 156 ነጥብ 05 ብር ሲሆን ዝቅተኛው የጨረታ ዋጋ ደግሞ 153 ነጥብ 8805 ብር ሆኗል። ባንኩ በዚህ ጨረታ አንድ ዶላርን 155 ነጥብ 88 ብር መሸጡን አስታውቋል። በዚሁ ጨረታ ላይ በአጠቃላይ 20 የንግድ ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ ካቀረቡት የዋጋ ተወዳዳሪነት አንጻር 9 ባንኮች ብቻ የቀረበውን የውጭ…
Read More
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የኢራንን ጥቃት አወገዙ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የኢራንን ጥቃት አወገዙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እሁድ ዕለት ኢራን በኩዌት ላይ የፈጸመችውን ጥቃት ተከትሎ ከኩዌት ልዑል አልጋ ወራሽ ሼክ ሳባህ ኻሊድ አል ሀማድ አል ሳባህ ጋር በስልክ መወያየታቸው ተገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከኩዌቱ ልዑል አልጋ ወራሽ ጋር ባደረጉት ውይይት በአገሪቱ ሉዓላዊ ግዛት እና የአየር ክልል ላይ የሚፈጸም ጥቃትን በጽኑ ማውገዛቸውን የኩዌት የዜና ወኪል ዘግቧል። ይህ በዚህ እንዳለም ኢራን በእስራኤል እና አሜሪካ በደረሰባት የአየር ላይ ጥቃት የአጸፋ እርምጃ በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ላይ በምትወስዳቸው እርምጃዎች ኢትዮጵያዊን መጎዳታቸው እየተገለጸ ይገኛል፡፡ በመቶ ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊን እስራኤልን ጨምሮ በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ተቀጥረው በመስራት ላይ ሲሆኑ ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኢምሬት፣ ኳታር፣ ኩዌት እና ባህሬን ብዙ ኢትዮጵያዊያን ይኖራሉ፡፡ ኢራን…
Read More