crimeinaddisababa

የራይድ ታክሲ ተጠቃሚ በመምሰል ሾፌሮችን ሲገድሉ የነበሩ አራት ግለሰቦች በሞት ተቀጡ

የራይድ ታክሲ ተጠቃሚ በመምሰል ሾፌሮችን ሲገድሉ የነበሩ አራት ግለሰቦች በሞት ተቀጡ

የታክሲ ኮንትራት በመጥራት ሹፌሮችን በመግደል ተሽከርካሪ ሲሰርቁ የነበሩ አራት ግለሰቦች በሞት እንዲቀጡ ውሳኔ ተላለፈባቸው በተለያዩ ጊዜያት አሽከርካሪዎችን  ራቅ ወዳለ ስፍራ እየወሰዱ በመግደል ተሽከርካሪዎችን ሲሰርቁ የነበሩ አራት ግለሰቦች በቁጥጥር  ስር ውለው በሞት እንዲቀጡ ውሳኔ ተላልፎባቸዋል። በአዲስ አበባ ገላን ክፍለ ከተማ፣ በሳሪስ እንዲሁም በቢሾፍቱ መኖሪያቸውን ያደረጉት ቴዎድሮስ ብርሃኔ እና  እዩኤል ቴዎድሮስ እንዲሁም በሌላ በኩል ተፈሪ ተስፋዬ እና ዩሃንስ አረፋ  የተባሉት ግለሰቦች  ከአዲስ አበባ ቢሾፍቱ በመመላለስ ድርጊቱን ሲፈጽሙ እንደነበር  የሸገር ከተማ አስተዳደር  ዓቃቢ ህግ ጽ/ቤት የተለያዩ ወንጀሎች ምርመራ ዓቃቢ ህግ አቶ ሚዴቅሳ አጋሩ  ተናግረዋል። አራት ግለሰቦች ከግል ተበዳዮች በኮንትራት በመውሰድ ከዋናው መንገድ ውጪ በማስውጣት የአሽከርካሪዎቹን ህይወት በማጣፋት ተሽከርካሪዎቹን ይዞ በመሰወር  ለተለያዩ ጋራዦች እና  ግለሰቦች በመሸጥ ድርጊቱን ሲፈጽሙ እንደነበር ተገልጿል። ቴዎድሮስ እና…
Read More
በኢትዮጵያ የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን በማተም ወንጀል የተጠረጠሩ ቻይናዊያን በቁጥጥር ስር ዋሉ

በኢትዮጵያ የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን በማተም ወንጀል የተጠረጠሩ ቻይናዊያን በቁጥጥር ስር ዋሉ

በርካታ መጠን ያላቸው የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያን በማስፋፋት ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ። ተጠርጣሪዎቹ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል። በኢትዮጵያ መዲና አዲስ አበባ ቻይናዊያን ባለሀብቶች ንብረት የሆነው ፀሃይ ሪል ስቴት በዚህ ወንጀል እጁ እንዳለበት ፖሊስ ገልጿል። ፖሊስ የሪል ኢስቴቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ኪያ ዦንግን ጨምሮ ዘጠኝ የውጭ ሀገራት ዜጎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል። ፖሊስ በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ካዋላቸው የውጭ ሀገራት ዜጎች ውስጥ ሶስት ኢትዮጵውያን ተጠርጣሪዎችም ተይዘዋል። ፖሊስ ሁሉንም ተጠርጣሪዎችን ፍርድ ቤት አቅርቦ ተጨማሪ ምርመራዎችን ለማድረግ የ14 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል። ፖሊስ…
Read More
በአዲስ አበባ የአንድ ወረዳ ስራ አስፈጻሚ ተገደሉ

በአዲስ አበባ የአንድ ወረዳ ስራ አስፈጻሚ ተገደሉ

በአዲስ አበባ የአንድ ወረዳ ስራ አስፈጻሚ ተገደሉ በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ አለባቸው አሞኜ በቢሮአቸው ውስጥ ተገደሉ። የክፍለ ከተማው ኮሚኒኬሽን ባሰራጨው መረጃ ፤ " አቶ አለባቸው አሞኜ ቢሯቸው ውስጥ ቁጭ ብለው የህዝብ አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ከአንድ ተገልጋይ በሽጉጥ ተገድለዋል። ክፍለ ከተማው ስለ ግድያው ተጨማሪ መረጃ ባያደርግም ግድያውን ፈጽማል የተባለለው ተጠርጣሪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል ብሏል። ክፍለከተማው ባወጣው መግለጫ " አቶ አለባቸው በስራ ቁርጠኝነት የሚታወቁ ናቸው" "በበርካታ መንግስታዊና ህዝባዊ ተግባራት አርዓያነት ያለው ስራ የሰሩና ያስተባበሩ አመራራችን ነበሩ " ሲል ገልጿል። አመራሩ በደረሰባቸው ጥቃት ወደ ህክምና ቦታ ቢወሰዱም ህይወታቸውን ማትረፍ እንዳልተቻለ ተገልጿል።
Read More