kidnapping

በኢትዮጵያ የሚኖሩ የስሪላንካ ዜጎችን ያገቱ ዜጎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በኢትዮጵያ የሚኖሩ የስሪላንካ ዜጎችን ያገቱ ዜጎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በኢትዮጵያ የስሪላንካ ኤምባሲ ተወካይ ግንቦት 23/2026 ለስራ ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሦስት ዜጎቹ እንደተሰወሩ እና ሲሪላንካ ከሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ተደውሎ እያንዳንዳቸው 30 ሺ ዶላር እንዲከፍሉ መጠየቃቸውን ግንቦት 26 ቀን 2026  በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ሪፖርት አደረጉ። በአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ምክትል ዋና ጠቅላይ መምሪያ ወንጀል ፈፃሚዎቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል የክትትልና የምርመራ ቡድን በማዋቀር ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ እንደገለጸው ከሌሎች የፀጥታ ጉዳይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በቴክኖሎጂ በመታገዝ ባሰባሰበው መረጃ ሦስቱ ግለሰቦች በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C- 40463/AA በሆነች ሱዚኪ ዲዛየር  መኪና ከኤርፖርት ተሳፍረው መሄዳቸውን አረጋግጧል። የክትትል ቡድኑ አባላት አሽከርካሪውን  ጨምሮ 2 ኢትዮጵያውያንን እና 4 የፓኪስታን…
Read More
በኦሮሚያ ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ ከ50 በላይ ሰዎች ታገቱ

በኦሮሚያ ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ ከ50 በላይ ሰዎች ታገቱ

በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች የታገቱትን ሰዎች ለማስለቀቅ ለእያንዳንዳቸው አንድ ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ ተጠይቀዋል በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ ባሳለፍነው ቅዳሜ ማለዳ ላይ ከአዲስ አበባ ወደ ባህርዳር በመጓዝ ላይ የነበሩ ከ50 በላይ መንገደኞች ታይተዋል ። እገታውን የፈጸሙት የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ናቸው የተባለ ሲሆን ለአንድ ሰው አንድ ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ የታጋች ቤተሰቦች ታጣቂዎቹ እየደወሉ መጠየቃቸው ተገልጿል። እገታው የተፈጸመበት ስፍራ ከኢትዮጵያ ዋና ከተማ 75 ኪሎ ሜትር ላይ ሲሆን የፌደራል ፖሊስም ሆነ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ታጣቂዎቹ በዜጎች ላይ እገታውን ሲፈጽሙ ማስጣል እንዳልቻለ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል ። በዚህ አካባቢ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች የሚያደርሱትን ጥቃት በመፍራት የሌሊት ጉዞ ከቆመ አንድ ዓመት እንዳለፈውም ነዋሪዎቹ…
Read More
በአዲስ አበባ ዙሪያ ባለችው ሱሉልታ ከተማ በርካታ ሰዎች በሸኔ ታጣቂዎች ታገቱ

በአዲስ አበባ ዙሪያ ባለችው ሱሉልታ ከተማ በርካታ ሰዎች በሸኔ ታጣቂዎች ታገቱ

በቅርቡ በተዋቀረው የሸገር ከተማ አስተዳደር ሥር በሚገኘው የሱሉልታ ክፍለ ከተማ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ታፍነው መወሰዳቸው ተገልጿል። ነዋሪዎቹ እንደገለጹት፤ በሱሉልታ ክፍለ ከተማ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በማለት በሚጠራው እና በመንግሥት “ኦነግ ሸኔ” በመባል በአሸባሪነት በተፈረጀው ታጣቂ ቡድን የሚፈጸሙ መሰል ድርጊቶች እየተበራከቱ መምጣታቸውን አስረድተዋል፡፡ በዚህም “ከአንድ ሳምንት በፊት በአንድ ምሽት ብቻ ከሱሉልታ ክፍለ ከተማ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን አካባቢ ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ቁጥራቸው ከ20 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በሸኔ ታጣቂዎች ታፍነው ተወስደዋል” ሲል አዲስ ማለዳ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡ ሰዎቹ በተወሰዱበት ዕለትም ምንም አይነት የመሳሪያ ድምጽ ባለመሰማቱ የጸጥታ አካላት ደርሰው ሊያስጥሏቸው እንዳልዳቻሉ ጠቅሰዋል። ረቡዕ ግንቦት 30 ቀን…
Read More