ዜና

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከያዝነው ዓመት የካቲት ወር ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ባሉት አምስት ወራት በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ ገደብ ጥላለች። ኢትዮጵያ የኢንተርኔት እገዳውን የጣለችው በቲክቶክ፣ ቴሌግራም፣ ፌስቡክ እና ዩቲዩብ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ነው። በኢንተርኔት እገዳው ምክንያትም ኢትዮጵያ 7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ማጣቷን የመብቶችና ዴሞክራሲ እድገት ማዕከል ገልጿል፡፡ “ፖለቲካዊ አለመረጋጋቶችን ተከትሎ፤ ከ2008 ወዲህ የበይነመረብ ግንኙነትን ማቋረጥ በኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣ ችግር ነው” ያለው ማዕከሉ፤ የበይነመረብ ግንኙነት መቋረጡ የዴሞክራሲና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕድገት ጸር መሆኑን አመላክቷል፡፡ መንግሥት ዋና ዋና የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች በኢትዮጵያ እንዳይጎበኙ እገዳ መጣሉ ሕጋዊ መሰረት የሌለው ነው ሲልም ገልጿል፡፡ የበይነመረብ ግንኙነት መቋረጥ ትኩረት ሊያገኝ ባለመቻሉም የሰብዓዊ መብቶች እሴቶችን እንዲሁም በሕገ መንግሥቱ የተጠበቁ…
Read More
በአዲስ አበባ የባለ ትዳሮች ፍቺ በ60 በመቶ ጨመረ

በአዲስ አበባ የባለ ትዳሮች ፍቺ በ60 በመቶ ጨመረ

በከተማዋ ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ከ4 ሺህ በላይ ትዳር መፍረሱ ተገልጿል የፈረሰው ትዳር ቁጥር ከአምናው ጋር ሲነጻጸር በ60 በመቶ ጨምሯል ተብሏል በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት 4 ሺህ 696 ትዳር በፍቺ መጠናቀቁ ተገልጿል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የነዋሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሴ እንደገለፁት በ2015 ዓ.ም ከማዕከል እስከ ወረዳ ለ2 ሚሊየን 239 ሺህ 713 ተገልጋዮች አገልግሎት ተሰጥቷል። ከዚህ ውስጥ 37 ሺህ 397 ጋብቻ እና 4 ሺህ 696 ፍቺ መሆኑን ተናግረዋል። ዘንድሮ የተመዘገበው የፍቺ መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር፥ የ60 በመቶ ብልጫ አለው ብለዋል። ለአብነትም በ2014 ዓ.ም 2 ሺህ 937 ፍቺ መመዝገቡን እና በ2015 ዓ.ም ወደ…
Read More
ኢትዮጵያ እና ግብጽ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአራት ወራት ውስጥ ችግራቸውን ለመፍታት ተስማሙ

ኢትዮጵያ እና ግብጽ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአራት ወራት ውስጥ ችግራቸውን ለመፍታት ተስማሙ

ግብጽ በሱዳን ያለውን ጦርነት ለማስቆም ያለመ ውይይት የጎረቤት ሀገራት መሪዎችን መጋበዟ ይታወሳል። ኢትዮጵያን ጨምሮ የሱዳን ጎረቤት ሀገራት በመድረኩ ላይ ለመሳተፍ ወደ ካይሮ ያመሩ ሲሆን ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከውይይቱ በተጓዳኝ ከፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ጋር መወያየታቸው ተገልጿል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ መወያየታቸው ሲገለጽ የግድቡ ውሀ አሞላል ደግሞ የመሪዎቹ ዋነኛ መወያያ እንደሆነ ተገልጿል። በዚህ መሰረትም ኢትዮጵያ በግድቡ ውሀ አሞላል ዙሪያ ግብጽን እና ሱዳንን የመጉዳት ፍላጎት የላትም የተባለ ሲሆን በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ተጨማሪ ውይይቶችን ለማድረግ ስለመስማማታቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳንም በህዳሴው ግድብ ውሀ አሞላል እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ያለባቸውን አለመግባባት በአራት ወራት ውስጥ በሚያደርጉት ውይይት ወደ…
Read More
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዳይሬክተር ከሀላፊነታቸው ለቀቁ

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዳይሬክተር ከሀላፊነታቸው ለቀቁ

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ጂማ ዲልቦ በገዛ ፈቃዳቸው ስራቸውን መልቀቃቸውን አስታውቀዋል። ዳይሬክተሩ ከአራት ዓመታ በላይ ከመሩት ተቋም ስራቸውን ለመልቀቅ ያቀረቡት ጥያቄ በመንግስት ተቀባይነት ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ኃላፊ ስራቸውን ለምን እንደለቀቁ ያሉት ነገር የለም። ጂማ ዲልቦ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ "ዘርፉ ከነበረበት ድባቴ ወጥቶ ለሀገር ልማትና ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ አስተዋጽኦ ማበርከት መጀመሩ በቀጣይ ዓመታት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተስፋ አደርጋለሁ" ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በጦርነት ምክንያት የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ቁጥር እያደገ የመጣ ቢሆንም በዛው ልክ ግን ሰራተኞቻቸው እየተገደሉባቸው መሆኑን መናገራቸው ይታወሳል። ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ብቻ ከ36 በላይ ለተቸገሩ ዜጎች ድጋፍ ለማድረስ በመንቀሳቀስ ላይ እያሉ እንደተገደሉ ተገልጿል።…
Read More
ኢትዮጵያ ለታራሚዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና መስጠት ጀመረች

ኢትዮጵያ ለታራሚዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና መስጠት ጀመረች

በኢትዮጲያ ለመጀመሪያ ጊዜ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት የመንጃ ፍቃድ ስልጠና መስጠት ተጀመረ አሁን ላይ 22 ታራሚዎች ስልጠናውን እየወሰዱ ይገኛል ተብሏል፡፡ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽነር ጀኔራል ዳመና ዳሮታ እንዳሉት ለመጀመሪያ ጊዜ በዝዋይ ማረሚያ ማዕከል ለታራሚዎች የአሽከርካሪ መንጃ ፍቃድ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል፡፡ ስልጠናው በማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽን ታሪክ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ማእከል የመጀመሪያው ሲሆን ታራሚዎች የእርምት ጊዜያቸውን ጨርሰው ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ በቀጥታ ወደ ስራ አለም እንዲገቡ የሚያግዝ ነው ተብሏል። ለመጀመሪያ ጊዜ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ማእከል ሲከፍት ለታራሚው እና ለፖሊስ አባላት እንዲያገለግል ታስቦ ሲሆን እስካሁን 22 ታራሚዎች ስልጠናውን እየወሰዱ ይገኛል። የህግ ታራሚዎችን በይበልጥ የሙያ ባለቤት የማድረግ ስራ በቀጣይ በማስፋፋት ከመንጃ ፍቃድ በተጨማሪ የመካኒክነት ስልጠናና የተሽከርካሪ…
Read More
በኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ቁልፍ ሰብረው እየገቡ መሆኑ ተገለጸ

በኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ቁልፍ ሰብረው እየገቡ መሆኑ ተገለጸ

በሸገር ከተማ አስተዳደር በሚገኘው ኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ለባለእድለኞች በተላለፉ ቤቶች ውስጥ ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ቁልፍ ሰብረው በመግባት ወረራ እየፈጸሙ መሆኑን የኮንዶሚኒየሙ ሕጋዊ ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ በኮንዶሚኒየሙ የእጣ እድለኞች ሆነው ለባለቤቶች ቁልፍ ተላለፈው፤ ነገር ግን ተቆልፈው በተቀመጡ ቤቶች እና እስካሁን ለባለእድለኞች ባልተላለፉ ቤቶች ላይ የማይታወቁ ሰዎች ወረራ እየፈጸሙ ነው ተብሏል። ይህን ድርጊት ለመከላከል ጥረት በሚያደርጉ የኮንዶሚኒየም የጥበቃ ሠራተኞች ላይም ዛቻ እና ማስፈራሪያ በማድረስ ሰዎቹ በኃይል እየገቡ መሆናቸውን አዲስ ማለዳ ዘግቧል፡፡ ነዋሪዎቹ አክለውም፤ “ተዘግቶ የተቀመጠን ቤት በኃይል ሰብረው ገብተው ወረራ ሲፈጽሙ አንድም የመንግሥት አካል ሊያሰቆማቸው የሞከረ የለም፡፡” ሲሉ ተደምጠዋል። ከመጋቢት 2015 ጀመሮ በኮንዶሚኒየሞቹ ላይ ከፍተኛ ወረራ እየተካሄደ መሆኑን በመጠቆምም፤ “ጉዳዩን ለሚመለከተው አካል በተደጋጋሚ…
Read More
በኢትዮጵያ ከ15 ሺህ በላይ የካንሰር ህመምተኞች የህክምና ወረፋ በመጠባበቅ ላይ መሆናቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከ15 ሺህ በላይ የካንሰር ህመምተኞች የህክምና ወረፋ በመጠባበቅ ላይ መሆናቸው ተገለጸ

የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ፤ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት ወረፋ የሚጠብቁ መኖራቸውን አስታውቋል። የሆስፒታሉ የካንሰር ሕክምና ማዕከል ክፍል ኃላፊ ዶክተር ኤዶም ሰይፉ እንዳሉት "የተለያዩ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠብቁ ከ2013 መጨረሻ፣ 2014 ዓ.ም. እና 2015 ዓ.ም. ወረፋ ያልደረሳቸው አሉ፡፡ ይሁን እንጂ በየዕለቱ የሚመጡ ድንገተኛ የካንሰር ታካሚዎች በመኖራቸው በቅድሚያ ለእነዚህ ታካሚዎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ ይደረጋል። በሆስፒታሉ ቆይተው መታከም ይችላሉ ተብለው የተለዩት ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ሕክምና ለማግኘት እየተጠባበቁ ያሉትን ለማስተናገድ ጥረት እየተደረገ ነውም ብለዋል። ለዚህ ወረፋ መብዛት ዋነኛ ምክንያት ብለው ያቀረቡት በሆስፒታሉ የሚገኘው መሣሪያ አንድ ብቻ በመሆኑ እንደሆነም ዶክተር ኤዶም ተናግረዋል። በዚህ ዓመት ብቻ በተደረገው ማጣራት የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠበባቁ 5,000…
Read More
በመተከል ዞን በጉምዝ ታጣቂዎች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 18 ደረሰ

በመተከል ዞን በጉምዝ ታጣቂዎች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 18 ደረሰ

በመተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ በጉምዝ ታጣቂዎች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 18 ደረሰ በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ በታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ 18 ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ግድያው የተፈጸመው አርብ ሰኔ 30 ቀን 2015 ሲሆን፤ ከ8 በላይ ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በሕክምና ላይ እንደሚገኙም ታውቋል፡፡ እንደነዋሪዎቹ ገለጻ ከሆነ የችግሩ መነሻ፤ አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለሥራ በወጣበት ተገድሎ በመገኘቱ አስከሬኑን ለማምጣት በሄዱ የጸጥታ አካላት ላይ በአካባቢው የሚገኙ የጉምዝ ታጣቂዎች ተኩስ በመክፈታቸው ሲሆን፤ በዚህም በርካታ ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል፡፡ ተኩሱን የከፈቱት ሽፍታ የነበሩ እና የሰላም ተመላሽ ተብለው ትጥቃቸውን ሙሉ ለሙሉ ለመንግሥት እንዲያስረክቡ ከተጠየቁ ታጣቂዎች መካከል ትጥቅ ያልፈቱ እና በጫካ የሚኖሩ ታጣቂዎች…
Read More
ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ለ31ኛ ጊዜ አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ለ31ኛ ጊዜ አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የዘንድሮውን የቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን አንስቷል። ባህርዳር ከነማ ውድድሩን በሁለተኝነት አጠናቋል። የ2015 የኢትዮጵያ ቤት ኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ አሸናፊነት ተጠናቋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊጉን በ64 ነጥብ አንደኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ ባህርዳር ከነማ ደግሞ በ60 እንዲሁም ኢትዮጵያ መድን በ49 ነጥቦች የውድድር ዓመቱን አጠናቀዋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ወይም ፈረሰኞቹ ፕሪምየር ሊጉን ለ31ኛ ጊዜ አሸናፊ ሆነዋል። የወራጅነት ደረጃዎች ላይ ደግሞ አርባምንጭ እግር ኳስ ክለብ በ34 ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ ክለብ በ18 እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ15 ነጥቦች ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርደዋል። የኮኮብ ግብ አግቢነት ደረጃውን የቅዱስ ጊዮርጊሱ እስማኤል አጎሮ በ25 የውድድር ዓመቱ ኮኮብ ግብ አግቢ ሆኖ አጠናቋል።
Read More
ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱ ዜጎች ቁጥር ከ60 ሺሕ በላይ ደረሰ

ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱ ዜጎች ቁጥር ከ60 ሺሕ በላይ ደረሰ

በሱዳን ብሑራዊ ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ ሀይል መካከል ያለውን ግጭት በመሸሽ ከ60 ሺሕ በላይ ሰዎች በአማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉምዝ እና በጋምቤላ ክልሎች በኩል ድንበር አቋርጠው ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት ገልጿል። በአጠቃላይ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡት መካከልም ከ30 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ከ15 ሺሕ በላይ የሚሆኑት ሱዳናውያን ሲሆኑ፤ ከ13 ሺሕ በላይ ያህሉ ደግሞ የሌላ አገር ዜጎች መሆናቸው ተጠቁሟል። የተባበሩት መንግሥታ ድርጅት በአገሪቱ በተቀሰቀሰው ግጭት ከ25 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አስቸኳይ የሰብአዊ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የገለጸ ሲሆን፤ በአገሪቱ ጾታዊ ጥቃት እየጨመረ መምጣቱን አስታውቋል። እንዲሁም ጦርነቱ ከተጀመረበት ባለፈው ሚያዚያ ወር አንስቶ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸውን፣ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውና ከግማሽ ሚሊዮን…
Read More