Prisoners'

ኢትዮጵያ በእስር ላይ ለሚገኙ ታሳሪዎች በቂ ምግብ እያገኙ አይደለም ተባለ

ኢትዮጵያ በእስር ላይ ለሚገኙ ታሳሪዎች በቂ ምግብ እያገኙ አይደለም ተባለ

በፌደራል ማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ ታራሚዎች በቀን ለአንድ ታራሚ የሚመደበው በጀት 35 ብር ብቻ በመሆኑ በቂ ምግብ እያገኙ እንዳልሆነ ተገልጿል፡፡ የተመደበው በጀት አነስተኛ መሆኑ እና የወቅታዊ የገበያ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ ለታራሚዎች የሚቀርብ ምግብ በቂ እንዳይሆን አድርጎታል ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፤ በቃሊቲ ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማእከል (በተለምዶ አባ ሳሙኤል) በመባል በሚጠራው ማረሚያ ቤት የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ጉብኝት ማድረጉን ተናግሯል፡፡ በዚህም ከምግብ አቅርቦት ማነስ በተጨማሪ አልፎ አልፎ አጃቢ የለም በማለት በቀጠሯቸው ፍርድ ቤት እና ሆስፒታል የማይወሰዱ ታራሚዎች እንዳሉም ባደረኩት ምልከታ ለማወቅ ችያለሁ ብሏል ኢሰመኮ፡፡ የአጃቢዎች እጥረት የሚፈጠረውም በማረሚያ ቤቱ የሰው ኃይል ቁጥር ማነስ እና የመርኃ ግብር መደራረብ…
Read More
ኢትዮጵያ ለታራሚዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና መስጠት ጀመረች

ኢትዮጵያ ለታራሚዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና መስጠት ጀመረች

በኢትዮጲያ ለመጀመሪያ ጊዜ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት የመንጃ ፍቃድ ስልጠና መስጠት ተጀመረ አሁን ላይ 22 ታራሚዎች ስልጠናውን እየወሰዱ ይገኛል ተብሏል፡፡ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽነር ጀኔራል ዳመና ዳሮታ እንዳሉት ለመጀመሪያ ጊዜ በዝዋይ ማረሚያ ማዕከል ለታራሚዎች የአሽከርካሪ መንጃ ፍቃድ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል፡፡ ስልጠናው በማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽን ታሪክ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ማእከል የመጀመሪያው ሲሆን ታራሚዎች የእርምት ጊዜያቸውን ጨርሰው ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ በቀጥታ ወደ ስራ አለም እንዲገቡ የሚያግዝ ነው ተብሏል። ለመጀመሪያ ጊዜ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ማእከል ሲከፍት ለታራሚው እና ለፖሊስ አባላት እንዲያገለግል ታስቦ ሲሆን እስካሁን 22 ታራሚዎች ስልጠናውን እየወሰዱ ይገኛል። የህግ ታራሚዎችን በይበልጥ የሙያ ባለቤት የማድረግ ስራ በቀጣይ በማስፋፋት ከመንጃ ፍቃድ በተጨማሪ የመካኒክነት ስልጠናና የተሽከርካሪ…
Read More