ኢኮኖሚ

ኢትዮጵያ በቴሌግራም መተግበሪያ ላይ ዳግም እገዳ ጣለች

ኢትዮጵያ በቴሌግራም መተግበሪያ ላይ ዳግም እገዳ ጣለች

በኢትዮጵያ የቴሌግራም መተግበሪያ የማህበራዊ ትስስር ገጽ ከዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 19 ቀን 2015ዓ.ም ጠዋት ጀምሮ እየሰራ አይደለም። ገደቡ የተጣለዉ ዛሬ ከሚጀመረዉ የ 2015 ዓ.ም የ 12ኛ ክፍል ፈተና ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። ይሁንና መንግሥት ለምን በቴሌግራም ላይ እገዳ እንደጣለ እስካሁን መረጃ ያልሰጠ ሲሆን መተግበሪያው በቪፒኤን እየሰራ ይገኛል። ከወራት በፊት በኦሮሚያ ክልል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አጋጥሟት የነበረዉን የመከፋፈል ድርጊትና የጳጳሳት ሹመነትን በሚመለከት በተለያዩ አካባቢዎች የተነሳዉን ተቋዉሞ ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እግዱ ተጥሎ ለአምስት ወራት መቆየቱ ይታወሳል። በዚህም መሰረት እንደ ፌስቡክ ፣ ቲክቶክ ፣ ቴሌግራም ፣ ኢንስታግራም ፣ ዩቲዩብ እና ሌሎች የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን ሰዎች VPN ( virtual private network )…
Read More
ኢትዮጵያ ወደ ውጪ ሀገራት ከተላከ የአህያ ስጋ 300 ሺህ ዶላር ማግኘቷን ገለጸች

ኢትዮጵያ ወደ ውጪ ሀገራት ከተላከ የአህያ ስጋ 300 ሺህ ዶላር ማግኘቷን ገለጸች

ቻይና ዋነኛዋ የኢትዮጵያ አህያ ስጋ የተላከባት ሀገር ስትሆን ፍላጎቱ እያደገ እንደሆነም ተገልጿል። በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ የአህያ ስጋን ወደ ሆንግኮንግ በመላክ 3 መቶ ሺህ ዶላር ገቢ ማግኘቷን የእንስሳት ልማት ኢንስትቲዩት አስታውቋል፡፡ በኢንስትቲዩቱ ምክትል ዋና  ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ሳህሉ ሙሉ እንደተናገሩት፣ ከአህያ ስጋ ውጪ የአህያ ቆዳን እንደ ቻይና ያሉ ሃገራት ለመድሃኒትነት በስፋት ሲጠቀሙበት የሚስተዋል በመሆኑ የስጋ ምርቱን ወደ ሆንግኮንግ እንዲላክ ተደርጓል ብለዋል፡፡ ገቢው  የተገኘውም በተጠናቀቀው በጀት አመት 140 ቶን የአህያ ስጋ ምርትን ወደ ውጪ ገበያ በመላክ እንደሆነ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ በበጀት አመቱ 600 ቶን የአህያ ስጋን ወደ ውጪ ለመላክ አስቀድሞ ታቅዶ እንደነበር ኢንስቲትዩቱ ገልጿል፡፡ በአህያ ስጋ የወጪ ንግድ  ዙሪያ የቄራ ድርጅቶች…
Read More
ሰላምዊት ዳዊት የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ ሆነው ተሾሙ

ሰላምዊት ዳዊት የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ ሆነው ተሾሙ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ሰላማዊት ዳዊትን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሀላፊ አድርገው ሾሙ። የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ሶስት ከፍተኛ አመራሮች ከሀላፊነት መነሳታቸው ተገልጿል። ፓስፖርት እና መሰል የዜግነት አገልግሎቶችን ለመስጠት የተቋቋመው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ተቋም ቅሬታዎች ሲቀርቡበት ቆይተዋል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ላለፉት አንድ ዓመት ከመንፈቅ የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎትን በዋና ዳይሬክተርነት ሲመሩ የነበሩት አቶ ብሩህተስፋ ሙልጌታን፣ በምክትል ዳይሬክተርነት ሲያገለግሉ የነበሩት ፍራኦል ጣፋ እና ታምሩ ግንበቶን ከኅላፊነት አንስተዋል። የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ህዝብ ግንኙነት እና ኮሙንኬሽን ሀላፊ ወይዘሮ ማስታዋል ገዳ ለአልዓይን እንዳሉት ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ከሰኔ 12 ቀን 2015 ዓም ጀምሮ ተቋሙን በዋና ዳይሬክተርነት እንዲመሩ መሾማቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ደርሶናል ብለዋል። እንዲሁም…
Read More
ኢትዮጵያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት ጠየቀች

ኢትዮጵያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት ጠየቀች

የኢትዮጵያ መንግስት ለሁለተኛው አገር በቀል የኢኮኖሚ ፕሮግራም ማስፈጸሚያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር ጠይቋል፡፡ ብድሩ እና እርዳታው የተጠየቀው የዓለም የገንዘብ ድርጅት አይኤምኤፍ፣ ዓለም ባንክና ኢትዮጵያ ያለባትን የውጭ ዕዳ መልሶ ከማሸጋሸግ ለማግኘት እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ተክለ ወልድ አጥናፉ ለሪፖርተር እንዳሉት ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከአሜሪካ፣ ፈረንሣይና ሌሎች ሀገራት ጋር ያላት ግንኙነት መልካም መሆኑ ብድሩ ሊገኝ ይችላል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የብድር መክፈያ ጊዜ እንዲስተካከል ጠይቃለች ያሉት አማካሪው ብድሩ ድርድር ከተደረገበት በኋላ ይለቀቃል የሚል ተስፋ መኖሩንም ጠቅሰዋል፡፡ የአሜሪካ ኮንግረስ ኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን ገደብ እ.ኤ.አ. በጁላይ ወር መጨረሻ ላይ ያነሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ፣ ይህም ገንዘቡን ለማግኘት ጥሩ እርምጃ ይሆናልም ተብሏል፡፡ 12 ቢሊዮን…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም 76 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ

ኢትዮ ቴሌኮም 76 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ

ቴሌብር የ680 ቢሊዮን ብር ግብይት መፈጸሙን ኢትዮ ቴሌኮም ገልጿል። የኢትዮ ቴሌሎም ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸምን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። ስራ አስፈጻሚዋ በመግለጫቸው እንዳሉት ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 76 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ገቢ ማግኘቱን ተናግረዋል። ከተገኘው አጠቃላይ ገቢ ውስጥም 44 በመቶው ከድምጽ ጥቅል ሲገኝ 23 በመቶው ከኢንተርኔት አገልግሎት መገኘቱን ስራ አስፈጻሚዋ አክለዋል። ተቋሙ ከውጭ ምንዛሬ አገልግሎቶች 164 ሚሊዮን ዶላር አግኝቷል ያሉት ፍሬህይወት የ4G ቴሌሎም አገልግሎት ያገኙ ከተሞች ቁጥርም ወደ 164 ከፍ ማለቱን ገልጸዋል። በአጠቃላይ የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር 72 ሚሊዮን ደርሷል የተባለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 34 ነጥብ 3 ሚሊዮን ያህሉ የቴሌብር ደንበኞች ናቸውም ብለዋል። በ2015 ዓ. ም…
Read More
ኢትዮጵያ ለቤተሰብ እቅድ አገልግሎት የ36 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

ኢትዮጵያ ለቤተሰብ እቅድ አገልግሎት የ36 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

በጀቱ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነ ተገልጿል። የ36 ሚሊዮን በጀት ስምምነቱ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት በኢትዮጵያ የቤተሰብ ዕቅድን ተደራሽ ለማድረግ ይውላል ተብላል። በኢትዮጵያ 22 በመቶ ሴቶች የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ተደራሽ ያልሆነላቸው ሲሆን በጀቱ ከዚህ አንጻር ተጨማሪ ሴቶችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል። በበጀት ስምምነቱ ላይ የተገኙት የጤና ጥበቃ ሚንስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳሉት የቤተሰብ እቅድ አገልግሎቱን ተደራሽነት ለማጠናከር እንቅፋት ከሆኑ ችግሮች መካከል አገልግሎቱ በነፃ የሚሰጥና ወጭው በአብዛኛው  በለጋሽ አካላት የሚሸፈን በመሆኑና ከለጋሽ አካላት የሚገኘው ድጋፍ እየቀነሰ መምጣቱ ነው ብለዋል። እንዲሁም በአለም አቀፍ ደረጃ የዋጋ ንረት በመኖሩ ለግብዓት የሚያስፈልግ የበጀት ዕጥረት ማጋጠሙን የጠቆሙት ሚንስትሯ ችግሩን በመቅረፍ አቅርቦቱን እንዳይቆራረጥ ለማድረግ  በመደበኛነት ከሚመደበው በጀት…
Read More
ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞችን ተከለች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ "በአንድ ቀን 567 ሚሊዮን ችግኞች ተተክሏል" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በዛሬው እለት 567 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል። በአንድ ቀን 500ሺ ችግኝ የመትከል ዘመቻ አማካኝነት በሀገሪቱ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ችግኝ ሲተክሉ የሚያሳዩ ፎቶዎች እና ቪዲዮዎች ተለቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የችግኝ ተከላው" ለኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት" ነው ሲሉ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዚህ አመት ብቻ ከካርቦን ሽያጭ 52 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቷን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የችግኝ ተከላው ስራ በዚሁ ከቀጠለ ከካርቦን ሽያጭ የምታገኘው ገቢ በእጥፍ እንደሚጨምር ገልጸዋል። ይሁንና በአንድ ጀምበር ተተከለ የተባለው የችግኝ መጠን በትክክል ስለመተከሉ በገለልታኛ አካል አልተረጋገጠም።
Read More
ቦይንግ ኩባንያ ከቲንክ ያንግ ጋር በመተባበር ለ60 ኢትዮጵያዊያን ስልጠና ሰጠ

ቦይንግ ኩባንያ ከቲንክ ያንግ ጋር በመተባበር ለ60 ኢትዮጵያዊያን ስልጠና ሰጠ

ለአራት ቀናት የተሰጠው ይህ ስልጠና ከቲንክ ያንግ እና ከአሜሪካው የአቪዬሽን ቦይንግ ኩባንያ ጋር በመተባበር ነው። ስልጠናው ከ20 ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ ለ60 ተማሪዎች በአዲስ አበባ ተሰጥቷል። ከሰባት ዓመት በላይ ጀምሮ እድሜ ላላቸው የተሰጠው ይህ ስልጠና ታዳጊዎች ከቴክኖሎጂ ጋር እየተዋወቁ እንዲያድጉ በማሰብ የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል። ለታዳጊዎቹ የተሰጠው የስልጠና አይነት ዌብሳይት ማበልጸግ፣ ሮቦቲንግ፣ ኮዲንግ እና አርቲፊሻል እንተለጀንስ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። ዓለም አቀፉ የአቪዬሽን ተቋም ቦይንግ የስልጠናው አካል ሲሆን የበጀት ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል። በቦይንግ ኩባንያ የመካከለኛው ምስራቅ፣ አፍሪካ እና ተርኪየ ፕሬዝዳንት የሆኑት ኩልጅት ጋታ ስልጠናው የቦይንግ ማህበራዊ ሀላፊነት አንዱ አካል ነው ብለዋል። "የኢትዮጵያ መንግሥት ድጅታል ኢኮኖሚ ለመገንባት የያዘውን እቅድ ለመደገፍ ወደ ኢትዮጵያ መጥተናል ያሉት"…
Read More
ኢትዮጵያ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የጣለችውን ገደብ አነሳች

ኢትዮጵያ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የጣለችውን ገደብ አነሳች

በኢትዮጽያ ለወራት ያህል በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ ተነስቷል። በኢትዮጵያ ከየካቲት ወር መጀመሪያ አንስቶ በኢንተርኔት አገልግሎቶች ማለትም በፌስቡክ፣ ሜሴንጀር፣ ቴሌግራም እና ቲክቶክ ላይ ገደብ መጣሉ ይታወሳል። በኢትዮጵያ የኢንተርኔት ገደብ መጣሉን ተከትሎ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንን ጨምሮ በርካታ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች መንግሥት ገደቡን እንዲያነሳ ሲጠየቅ ቆይቷል። በኢንተርኔት እገዳው ምክንያትም ኢትዮጵያ 7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ማጣቷን የመብቶችና ዴሞክራሲ እድገት ማዕከል ገልጿል፡፡ “ፖለቲካዊ አለመረጋጋቶችን ተከትሎ፤ ከ2008 ወዲህ የበይነመረብ ግንኙነትን ማቋረጥ በኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣ ችግር ነው” ያለው ማዕከሉ፤ የበይነመረብ ግንኙነት መቋረጡ የዴሞክራሲና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕድገት ጸር መሆኑን አመላክቷል፡፡ መንግሥት ዋና ዋና የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች በኢትዮጵያ እንዳይጎበኙ እገዳ መጣሉ ሕጋዊ መሰረት…
Read More
ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለማችን ቀዳሚ ተከፋይ ስፖርተኛ ሆነ

ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለማችን ቀዳሚ ተከፋይ ስፖርተኛ ሆነ

የአልናስር አጥቂ የሆነው ፖርቹጋላዊው ክርስቲያኖ ሮናልድ የ2023 ከፍተኛ ተከፋይ ስፖርተኛ ሆኖ ተመዝግቧል። እንደ ፎርብስ ዘገባ ከሆነ የአምስት ጊዜ ባሎንዶር ተሸላሚው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በተያዘው ዓመት ብቻ 136 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል። የዓለም ዋንጫ አሸናፊው አርጀንቲናዊው ሊዮኔል ሜሲ በ2022 ዓመት 130 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ ተከፍሎታል። ክርስቲያኖ ካገኘው የ136 ሚሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢ ውስጥ 90 ሚሊዮን ዶላሩን ከሜዳ ውጪ ማለትም ከማስታወቂያ እና ስፖንሰር ስራዎች ማግኘቱ ተገልጿል። በማንችስተር ዩናይትድን ባለ መግባባት ወደ ሳውዲ አረቢያው አልናስር ያመራው ክርስቲያኖ ሮናልዶ ደመወዙ እጥፍ እንዳደገለትም ተገልጿል። በአጠቃላይ በስፖርቱ ዘርፍ ሊዮኔል ሜሲ እና ክሊያን ምባፔ ከክርስቲያኖ ሮናልዶ በመቀጠል ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዱረጃን ይዘዋል። የቅርጫት ኳስ ኮኮቡ ለቦርን 119 ሚሊዮን…
Read More