Gonder

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አማራ ክልል የሚያደርጋቸውን በረራዎች ሰረዘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አማራ ክልል የሚያደርጋቸውን በረራዎች ሰረዘ

አየር መንገዱ በድረገጹ እንዳስታወቀው ወደ ደሴ፣ ጎንደር፣ባህርዳር እና ላሊበላ የሚያደርገውን በረራ ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ የተሰረዙት በረራዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ሊያደርጋቸው የነበሩ በረራዎች እንደሆኑ ገልጾ አየር መንገዱ ወደ ተጠቀሱት አካባቢዎች ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ ደንበኞች በረራዎቹ እንደተመለሱ አስተናግዳለሁም ብሏል፡፡ ወደሥፍራው ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ መንገደኞች ትኬታቸው ለአንድ ዓመት ያህል የሚያገለግል መሆኑን አውቃችሁ ወደፊት በፈለጋችሁት ቀን ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ መቀየር ትችላላችሁም ብሏል፡፡ ገንዘቡን መመለስ እንፈልጋለን ለሚሉ ደንበኞችም ገንዘብ መመለስ እንደሚቻል ገልጾ በአቅራቢያችሁ ባሉ የአየር መንገዱ ቲኬት ቢሮዎች በመሄድ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚቻልም አስታውቋል፡፡ ይሁንና አየር መንገዱ በምን በረራዎቹን እንደሰረዘ ያልገለጸ ሲሆን በአማራ ክልል እየተካሄዱ ባለው ጦርነት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ በረራውን ሰረዘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ በረራውን ሰረዘ

አየር መንገዱ በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ባሰራጨው መረጃ ወደ ደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ የሚያደርገውን በረራ ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ የተሰረዙት በረራዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ሊያደርጋቸው የነበሩ በረራዎች እንደሆኑ ገልጾ አየር መንገዱ ወደ ተጠቀሱት አካባቢዎች ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ ደንበኞች በረራዎቹ እንደተመለሱ አስተናግዳለሁም ብሏል፡፡ ይሁንና አየር መንገዱ በምን በረራዎቹን እንደሰረዘ ያልገለጸ ሲሆን በአማራ ክልል እየተካሄዱ ባለው ጦርነት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል በተከሰተው የጸጥታ ችግር ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጁ ይታወሳል፡፡ በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የህግ ማስከበር ስርአት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት መጠየቁ ይታወሳል። በአማራ ክልል በርካታ ከተሞች…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ላሊበላ እና ጎንደር የነበረውን በረራ ሰረዘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ላሊበላ እና ጎንደር የነበረውን በረራ ሰረዘ

በአማራ ክልል በርካታ ከተሞች በሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ውጊያ እየተካሄደ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ውጊያ ከተጀመረ ሳምንታትን ያስቆጠረ ሲሆን ንጹሃን የጉዳት ሰለባ እየሆኑ እንደሆነም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ ተናግረዋል፡፡ አቶ ክርስቲያን አክለውም የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አስተዳድር በአማራ ክልል የተለያዩ ቦታዎች በህዝብ ላይ ተኩስ ከፍቷል ብለዋል፡፡ የግጭቱ መነሻ የአማራ ክልል ልዩ ሀይል ለምን ይፈርሳል በሚል እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን የቀድሞ ልዩ ሀይል አባላት እና የፋኖ ታጣቂዎች ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጋር ውጊያ ውስጥ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡ የፋኖ ታጣቂዎች ቀስ በቀስ ወረዳዎችን እና ከተሞችን እየተቆጣጠሩ መምጣታቸውን ተከትሎ በታጣቂዎቹ…
Read More
ለ15ኛ ጊዜ ሎተሪ የደረሳቸው የጎንደሩ እድለኛ አባት

ለ15ኛ ጊዜ ሎተሪ የደረሳቸው የጎንደሩ እድለኛ አባት

ግለሰቡ በአንድ ዓመት ውስጥ የገናን እና ፋሲካ በዓል ሎተሪን አሸንፈዋል አቶ መሃመድ አህመድ አህመድ ይባላሉ፤ተወልደው ያደጉት ጎንደር ነው፡፡ አቶ መሃመድ ሙሉ ስማቸው መሃመድ አህመድ ቢሆንም በተደጋጋሚ ሎተሪ ስለጎበኛቸው የአባታቸው ስም ወደ ሎተሪ ተቀይሮ በሚኖሩበት ከተማ መሃመድ ሎተሪ እየተባሉ በመጠራት ላይ ናቸው፡፡ አቶ መሃመድ ሎተሪ 15 ጊዜ የሎተሪ እድል አሸናፊ መሆናቸውን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር መረጃ ያመላከታል፡፡ ከ1977 አመት ጀምሮ እስከ 2007 ዓ.ም ድረስ ሎተሪ ቆርጠው ያጡት ብር እንደሌለ እኝህ አባት ይናገራሉ፡፡ አቶ መሃመድ ከ500 ብር ጀምሮ እስከ 75ሺህ ብር ድረስ አሸናፊ ሆነዋል፡፡ የእኝህ አባት እድለኝነት የሚያስገርመው ደግሞ የገና ሎተሪ እጣ አሸናፊ ሆነው በዛው አመት በፋሲካም አሸናፊ መሆናቸው ነው፡፡ በሎተሪ ተስፋ ቆርጠው…
Read More
ኢትዮጵያን የጉዛራ ቤተ መንግሥት በ35 ነጥብ ስምንት ሚሊየን ብር ጥገና ሊደረግለት ነው

ኢትዮጵያን የጉዛራ ቤተ መንግሥት በ35 ነጥብ ስምንት ሚሊየን ብር ጥገና ሊደረግለት ነው

በዓለም ቅርስነት የተመዘገበው በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚገኘው የጉዛራ ቤተመንግሥት ከተደቀነበት የመፍረስ አደጋ ለመታደግ፤ ከፌደራል መንግሥት በተበጀተ 35 ሚሊዮን 800 ሺሕ ብር በጀት የጥገና ሥራው በዛሬው ዕለት እንደሚጀመር ተገልጿል። የጥገና ሥራው በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የጎንደር ዙሪያ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት የቅርስ ጥበቃና ቱሪዝም ልማት ቡድን መሪ ግርማቸው ሙሉጌታ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። ጉዛራ ቤተመንግሥት በጣና ተፋሰስ አካባቢዎች የሚገኝ የመጀመሪያው ቤተመንግሥት እንደሆነ ይነገራል። ጉዛራ ቃሉ የግዕዝ ሲሆን፤ ትርጉሙም ምቹ ማለት ነው። በጎንደር የነገሥታት ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን የጉዛራን ቤተመንግሥት የመሰረቱትም ያሳነፁትም ኢትዮጵያን ከ1556-1589 ድረስ በመሩት በአፄ ሰርፀ ድንግል መሆናቸው በፁሁፍ የሰፈሩ ማስረጃዎች ያሳያሉ። የጉዛራ ቤተመንግሥት ከእንፍራንዝ በስተደቡብ 5 ኪሎሜትር ወጣ ብሎ የተሰራ…
Read More