Flights

በአዲስ አበባ ያለው ከባድ አየር ንብረት የአውሮፕላን በረራዎችን አስተጓጎለ

በአዲስ አበባ ያለው ከባድ አየር ንብረት የአውሮፕላን በረራዎችን አስተጓጎለ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲስ አበባ በተከሰተው ከፍተኛ ጭጋጋማ አየር ምንክንያት ወደ ሌላ አየር ማረፊያዎች እያዘዋወረ መሆኑን አስታወቀ በአዲስ አበባ በተከሰተዉ ከፍተኛ ጭጋጋማ አየር አብዛኛው በረራዎች ቦሌ አዉሮፕላን ማረፊያ ሊያርፍ ባለመቻሉ ምክንያት ወደ ሌላ አየር ማረፊያዎች እንዲቀየሩ መደረጉን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል ። አየር መንገዱ እንደገለፀው ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ባለዉ ከፍተኛ ጭጋግ ( ጉም) ምክንያት የአየር ማረፊያዎችን ወደ ሌላ ቦታ እያዘዋወረ መሆኑን እና ይህም በሀገር ዉስጥ እና በአለም አቀፍ በረራዎች ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል ብሏል። በተጓዦች ላይ ለደረሰዉ መጉላላት ይቅርታ የጠየቀው አየር መንገዱ በተጓዦች ላይ ሊደርሱ የሚችሉ መጉላላቶችን ለመቀነስ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አውሮፕላን ጣቢያ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ በረራውን ሰረዘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ በረራውን ሰረዘ

አየር መንገዱ በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ባሰራጨው መረጃ ወደ ደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ የሚያደርገውን በረራ ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ የተሰረዙት በረራዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ሊያደርጋቸው የነበሩ በረራዎች እንደሆኑ ገልጾ አየር መንገዱ ወደ ተጠቀሱት አካባቢዎች ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ ደንበኞች በረራዎቹ እንደተመለሱ አስተናግዳለሁም ብሏል፡፡ ይሁንና አየር መንገዱ በምን በረራዎቹን እንደሰረዘ ያልገለጸ ሲሆን በአማራ ክልል እየተካሄዱ ባለው ጦርነት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል በተከሰተው የጸጥታ ችግር ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጁ ይታወሳል፡፡ በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የህግ ማስከበር ስርአት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት መጠየቁ ይታወሳል። በአማራ ክልል በርካታ ከተሞች…
Read More