Authomobil

ኢትዮጵያ በ34 ሚሊዮን ዶላር አዲስ ተሽከርካሪዎችን ልትገዛ መሆኗን አስታወቀች

ኢትዮጵያ በ34 ሚሊዮን ዶላር አዲስ ተሽከርካሪዎችን ልትገዛ መሆኗን አስታወቀች

የቻይና ሶስት ኩባንያዎች 312 ተሽከርካሪዎችን ለኢትዮጵያ ለመሸጥ ተስማሙ የቻይናዎቹ ዞሆንግቶን ሻንዚ እና ሻንጋይ የተሰኙ የአውቶሞቲቭ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ተሽከርካሪዎችን ለመግዛት ያወጣችውን ዓለም አቀፍ ጨረታዎችን አሸንፈዋል ተብሏል። ኢትዮጵያ ለተሽከርካሪዎቹ ግዢ 34 ሚሊዮን ዶላር በጀት መመደቧ ተገልጿል። የመንግስት ግዥ አገልግሎት በገንዘብ ሚኒስቴር ጠያቂነት ለፌዴራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶች እና ለመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች አገልግሎት የሚውሉ ተሽከርካሪዎችን ለመግዛት ጨረታ አውጥቶ ነበር። ሊገዙ የታሰቡት ተሽከርካሪዎች ብዛታቸው 312 ሲሆኑ በኤሌክትሪክና በነዳጅ የሚሰሩ እንደሆኑም ተገልጿል። ለተሽከርካሪዎች ግዢ 34 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላር ወጪ ይደረጋል የተባለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 33ቱ የኤሌክትሪክ ሚኒባስ ናቸው ተብሏል። የቻይናው ዞሆንግቶን የተሰኘው ኩባንያ 47 በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ሚኒባሶችን በሶስት ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር ለኢትዮጵያ ለማስረከብ ጨረታውን እንዳሸነፈ ተገልጿል።…
Read More
ኢትዮጵያ ቮልስዋገን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ አገደች

ኢትዮጵያ ቮልስዋገን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ አገደች

በቻይና የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ በጊዜያዊነት ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ማገዷን አስታውቃለች፡፡ በቻይና ሀገር የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ በቻይና ሀገር ተገጣጥሞ ወደ ኢትዮጵያ እየገባ የሚገኘው ቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሕጋዊ የሆነ ፈቃድ አለመኖሩን የጀርመኑ ኩባንያ በኤንባሲው በኩል በደብዳቤ ለሚኒስቴሩ ማሳወቁ ተገልጿል፡፡ በመሆኑም በቻይና ሀገር የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ከኩባንያው ሕጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስከሚረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ ታግዷል፡፡ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ተሽከርካሪዎች ላይ ክትትል በማድረግና የሕጋዊነት ማረጋገጫ መረጃዎችን የማጥራት ስራም በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተሠራ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ መንግስት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በስፋት እንዲመረቱ፣ እንዲገጣጠሙና ወደ ሀገር…
Read More